Monday, August 10, 2026

ለኒያላ ኢንሹራንስ አክሲዮን ማህበር ባለአክሲዮኖች በሙሉ

ዕጩ የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት ጥቆማ ለመቀበል የወጣ ማስታወቂያ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የኩባንያውን የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት ጥቆማ እና ምርጫ በአስመራጭ ኮሚቴ አማካኝነት እንዲከናወን በደነገገው መሰረት የኒያላ ኢንሹራንስ አ.ማ. ባለአክሲዮኖች ኅዳር 17 ቀን 2017 ዓ.ም. ባካሄዱት 30ኛ መደበኛ ስብሰባ በ2018 ዓ.ም. ለሚመረጠው ቦርድ 5 አባላት ያለው የቦርድ አስመራጭ ኮሚቴ መምረጣቸው ይታወሳል፡፡

በዚሁ መሰረት ኮሚቴው ዕጩ የቦርድ አባላትን ጥቆማ ከሰኔ 22 ቀን 2017 ዓ.ም እስከ መስከረም 22 ቀን 2018 ዓ.ም. ብቻ የሚቀበል ስለሆነ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መመሪያ SIB/32/2012 እና SIB/48/2019 ላይ የተመለከቱ የሚከተሉትን መስፈርቶችን የሚያሟሉ ዕጩ የቦርድ አባላትን እንድትጠቁሙ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡፡

  1. የኩባንያው ባለአክሲዮን የሆነ/ች
  2. ከነባር የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት የአገልግሎት ዘመናቸው ያላበቃ
  3. የኩባንያው ሰራተኛ ያልሆነ
  4. እድሜው 30 ዓመትና ከዚያ በላይ የሆነ/ች
  5. በሌላ የፋይናንስ ተቋም የዳይሬክተሮች ቦርድ አባል ያልሆነ/ች
  6. የትምህርት ደረጃ፡

                ሀ) ቢያንስ 75% የሚሆኑት የመጀመሪያ ዲግሪ ያላቸው

                ለ) የቀሩት 25% ቢያንስ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ያጠናቀቁ መሆን አለባቸው፡፡

  • የእምነት ማጉደል ወይም የማጭበርበር ተግባር ያልፈጸመ/ች፤ ለፋይናንሻል ተቋማትና ለተቆጣጣሪ አካል ሀሰተኛ መረጃ ያልሰጠ/ች፣ ስነ ምግባር ደንቦችን ባለማክበር የስነ-ስርአት እርመጃ ያልተወደበት/ባት፣ በሙስና ወንጀል ተከሶ ያልተፈረደበት/ባት እና ከመምረጥ መብት ያልተገደበ/ች
  • በንግድ ስራና በንግድ ስራ አስተዳደር በተለይም በኢንሹራንስ ዘርፍ የስራ ልምድ ያለው/ያላት (ቢሆን ይመረጣል)
  • በራሱ ወይም በሚመራው ወይም ዳይሬክተር በሆነበት ድርጅት ላይ የመክሰር ክስ ያልቀረበበት/ባት ወይም የኪሳራ ውሳኔ ያልተሰጠበት/ባት
  • በኪሳራ ምክንያት ንብረቱ ለእዳ ማቻቻያ ያልተወሰደበት/ባት
  • በታክስ ማጭበርበር ወንጀል ተከሶ ጥፋተኛ ያልተባለ/ች
  • የሚመራው/የምትመራው ወይም ዳይሬክተር የሆነበት/የሆነችበት ድርጅት ከገንዘብ ተቋማት የተበደረውን ገንዘብ ባለመክፈሉ ብድሩ ወደ ጤናማ ያልሆነ የብድር ደረጃ ያልዞረበት/ባት
  • የባንክ ብድር ባለመክፈሉ/ሏ ምክንያት ንብረቱ/ቷ በሀራጅ ያልተሸጠ
  • ሌሎች በመመሪያዎች የተገለጹ መስፈርቶችን የሚያሟሉ መሆን አለባቸው፡፡

የእጩ አባላት ተጠቋሚዎች ብዛት 18 ሲሆን ከእነዘህ መካከል 1/3ኛው ማለትም 6 እጩዎች በኩባንያው ውስጥ ያላቸው የአክሲዮን ይዞታ ከ2% በታች በሆኑ ወይም ተጽእኖ ፈጣሪ ባልሆኑ ባለአክሲዮኖች የሚጠቆሙና የሚመረጡ ሲሆን ቀሪዎቹ 12ቱ ደግሞ በሁሉም ባለአክሲዮኖች የሚጠቆሙና የሚመረጡ ይሆናሉ፡፡

ማሳሰቢያ፡-

በአግባቡ የተሞላውን የጥቆማ ቅጽ በቀጥታ ዋና መ/ቤት ማድረስ፣ ወይም በመ/ሳ/ቁ 12753 አዲስ አበባ ወይም በፋክስ ቁጥር 011-6-626706 ወይም በኢ-ሜይል nisco@nyalainsurance.com ወይም nisco@ethionet.et በተሰጠው የጊዜ ገደብ መላክ ይቻላል፡፡

የዳይሬክተሮች ቦርድ አስመራጭ ኮሚቴ

Hot this week

Production up, but the ‘cost’ variable weighs heavily

Production is up in 2021 for the Italian agricultural...

Luminos Fund’s catch-up education programs in Ethiopia recognized

The Luminos Fund has been named a top 10...

Well-planned cities essential for a resilient future in Africa concludes the World Urban Forum

The World Urban Forum (WUF) concluded today with a...

Private sector deemed key to unlocking AfCFTA potential

The private sector’s role is vital to fully unlock...

Africa faces trade crossroads as AGOA expiry nears

African governments, exporters and business leaders are preparing for...

Djibouti urged to tighten debt controls

A new economic assessment recommends that Djibouti implement tighter...

Who benefits from the migrant chaos in Spain?

What happened in the North African Spanish enclave of...

Childcare seen as economic infrastructure, not just welfare

Childcare should be treated as a core economic investment...

The Commercialization of Hope

Hope has always occupied a unique place in human...

MPs Warn Insecurity Could Jeopardize Elections

South Sudanese lawmakers warned on Wednesday that worsening insecurity...

Death Row Inmates Desperate to Escape Execution in Saudi Arabia Call the BBC

. ... Other foreigners, including Pakistanis, Sudanese and Jordanians,...

Addis Standard Editor-in-Chief Abducted, Offices Raided, Equipment Seized

JAKENN Publishing PLC, publisher of Addis Standard tri-lingual publications,...
spot_img

Related Articles

Popular Categories

spot_imgspot_img