የግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ አ.ማ. የባለአክስዮኖች 13ኛ መደበኛ እና 5ኛ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤዎች በኢትዮጵያ የንግድ ሕግ አንቀጽ 366(1) ፣ 367(1)፣ 370፣ 371(1) እና 400 እንዲሁም በባንኩ መመስረቻ ጽሑፍ አንቀጽ 20 እና 21 መሠረት ቅዳሜ ታህሳስ 04 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡00 ሰዓት ጀምሮ በአዲስ አበባ ከተማ ፒያሳ አካባቢ በሚገኘው የአድዋ ድል መታሰቢያ የፓን አፍሪካ አደራሽ ስለሚካሄድ የተከበራችሁ የባንኩ ባለአክስዮኖች በዕለቱ በጉባኤዎቹ ላይ እንድትገኙ የባንኩ የዳይሬክተሮች ቦርድ በአክብሮት ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡
1. ስለ አክሲዮን ማህበሩ መግለጫ
1.1. የአክሲዮን ማህበሩ ስም፡- ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ አ.ማ.
1.2. የዋና መስሪያ ቤት አድራሻ፡- አዲስ አበባ ከተማ፣ ቂርቆስ ክ/ከተማ ፣ ወረዳ 07
1.3. የንግድ ምዝገባ ቁጥር፡- KK/AA/3/0005948/2006
1.4. የሥራ ፍቃድ ቁጥር፡- LBB/018/2012
1.5. የተፈረመ ካፒታል፡- ብር 5,000,000,000.00
1.6. የተከፈለ ካፒታል፡- ብር 5,000,000,000.00
1.7. የባንኩ ድረ ገጽ፡- https://www.globalbankethiopia.com/
2. የ13 ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ አጀንዳዎች
2.1. የጉባኤውን አጀንዳ ማጽደቅ፣
2.2. እ.ኤ.አ. በ2024/25 የሂሳብ ዓመት የተደረጉ የአክሲዮን ዝውውሮችንና አዳዲስ አክሲዮኖችን ሽያጭ ማሳወቅ፣
2.3. እ.ኤ.አ. የ2024/25 ሂሳብ ዓመት የዳይሬክተሮች ቦርድን ሪፖርት ማድመጥ፣
2.4. እ.ኤ.አ. የ2024/25 ሂሳብ ዓመት የውጭ ኦዲተሮችን ሪፖርት ማድመጥ፣
2.5. በተራ ቁጥር 2.3 ላይ በቀረበው የዳይሬክተሮች ቦርድ ሪፖርት ላይ ተወያይቶ ማጽደቅ፣
2.6. በተራ ቁጥር 2.4 ላይ በቀረበው የውጭ ኦዲተሮች ሪፖርት ላይ ተወያይቶ ማጽደቅ፣
2.7. እ.ኤ.አ. በ2024/25 የሂሳብ ዓመት የተጣራ ትርፍ ክፍፍል በቀረበው የውሳኔ ሃሳብ ላይ ተወያይቶ መወሰን፣
2.8. እ.ኤ.አ. ከ2025/26 እስከ 2027/28 የሂሳብ ዓመታት የውጭ ኦዲተር መሾምና የአገልግሎት ክፍያውን መወሰን እና
2.9. እ.ኤ.አ. የ2024/25 ሂሳብ ዓመት የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላትን ዓመታዊ የስራ ዋጋ እና እ.ኤ.አ. የ2025/26 ሂሳብ ዓመት ወርሃዊ የአበል ክፍያ መወሰን ናቸው።
3. የ5ኛ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ አጀንዳዎች
3.1. የጉባኤውን አጀንዳ ማጽደቅ፣
3.2. የባንኩን ካፒታል ለማሳደግ በዳይሬክተሮች ቦርድ በቀረበው የውሳኔ ሃሳብ ላይ ተወያይቶ መወሰን እና
3.3. የባንኩን መመስረቻ ጽሑፍ ማሻሻል ናቸው።
4. ማሳሰቢያ
4.1. በጉባኤው ላይ በአካል መገኘት የማይችሉ ባለአክስዮኖች ይህ የጥሪ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እሰከ ታህሳስ 01 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ድረስ ከኢትዮጵያ ሆቴል በስተጀርባ ናሽናል ታወር ከሚገኘው የባንኩ ዋና መስሪያ ቤት 9ኛ ፎቅ ፋይናንስና አካውንትስ መምሪያ አክሲዮን (ሼር) ክፍል በመገኘት የዉክልና ቅጽ በመሙላት ወይም ውል ለማዋዋል ሥልጣን ካለው አካል በጉባኤው ላይ ለመገኘት እና ድምጽ ለመስጠት የሚያስችል የተሰጠ የውክልና ማስረጃ ዋናውንና አንድ ቅጅ ይዞ በመምጣት በጉባኤው ላይ መሳተፍ የሚችሉ መሆኑን በአክብሮት እየገልጽን የባንኩ የአክሲዮን ባለቤቶች ራሳቸው መጥተው በጉባኤው ላይ እንዲሳተፉ እናበረታታለን።
4.2. የባንኩ ባለአክሲዮኖች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በጉባኤው ላይ ለመሳተፍ ሲመጡ ማንነታቸውን የሚያሳይ የብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ (ፋይዳ)፤ የታደሰ የቀበሌ መታወቂያ ወይም ፓስፖርት ወይም መንጃ ፍቃድ ይዛችሁ እንዲትቀርቡ፣ እንዲሁም ትውልደ ኢትዮጵያውያን የውጭ ሀገር ዜግነት ያላቸው የባንኩ ባለአክሲዮኖች ይህንኑ የሚያረጋግጥ ቀኑ ያላለፈበት መታወቂያ (ቢጫ ካርድ) ይዘው መቅረብ እንዳለባቸው እናሳውቃለን፡፡
4.3. በተጨማሪም የድርጅት ተወካዮች፤ የድርጅቱ ሥራ አስኪያጅ ወይም ተመሳሳይ የኃላፊነት ደረጃ ላይ ያሉ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ ማስረጃ ወይም ድርጅቱን ወክለው እንዲገኙ የሚያረጋግጥ የተመዘገበ ቃለጉባኤ ወይም ውል ለማዋዋል ሥልጣን ካለው አካል የተሰጠ የውክልና ሰነድ ይዘዉ መቅረብ ያለባቸው መሆኑን እንገልጻለን፡፡
4.4. በስራ ላይ ያሉ የባንኩ የቦርድ አባላት እና ሠራተኞች በየትኛውም የባለአክሲዮኖች ጉባኤ ላይ ማንኛውንም ባለአክሲዮን ወክለው መሳተፍ አይችሉም።
የግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ አ.ማ. ዳይሬክተሮች ቦርድ






