Thursday, May 7, 2026

ሲቪል ማኅበራት ያላቸውን ሀብት አስመዝግበው እንዲልኩ ቀነ ገደብ ተሰጠ

የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶችን የሚከታተለውና የሚቆጣጠረው ባለሥልጣን፣ በሲቪል ማኅበራት ዘርፍ ለሚንቀሳቀሱ 100 ተቋማት የንብረት ምዝገባ እንዲያካሂዱ ጥብቅ ማስጠንቀቂያ አስተላለፈ። ከእነዚህም መካከል 70 የሚሆኑት የውጭ ድርጅቶች ይገኙበታል። ድርጅቶቹ ንብረታቸውን መዝግበው እንዲልኩ የተሰጠው ቀነ ገደብ እስከ ህዳር 13 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ነው።

ባለሥልጣኑ ለድርጅቶቹ በላከው ደብዳቤ ላይ እንዳስረዳው፣ የንብረት ምዝገባው የሲቪል ማኅበራት በሕግ የተሰጣቸውን የንብረት ባለቤትነት መብት ሳይነካ፣ የሕዝብ ሀብት አጠቃቀም ማረጋገጫ እና  የዘርፉን አጠቃላይ መረጃ ማጠናቀር የሚሉት ዓላማዎችን ለማሳካት ያለመ መሆኑ ተጠቁሟል።

በአዋጅ ቁጥር 1113/2011 መሰረት፣ በሕዝብ ስም የተሰበሰበው ሀብት ለታለመለት የሕዝብ ዓላማ መዋሉን የማረጋገጥ ግዴታ በባለሥልጣኑ ላይ የሚጣል ሲሆን፣ ይህንን ግዴታ ለመወጣት የንብረት ምዝገባው ወሳኝ መሆኑን አስረድቷል።

በአገር ደረጃ በሲቪል ማኅበረሰብ ዘርፍ ስር ምን ያህል የሚንቀሳቀስና የማይንቀሳቀስ ንብረት እንዳለ ጥቅል መረጃ ለመያዝ፣ ለመሰብሰብና ለማጠናቀር የምዝገባው ሂደት እንደሚያስፈልግ ተገልጿል።

Hot this week

Production up, but the ‘cost’ variable weighs heavily

Production is up in 2021 for the Italian agricultural...

Luminos Fund’s catch-up education programs in Ethiopia recognized

The Luminos Fund has been named a top 10...

Well-planned cities essential for a resilient future in Africa concludes the World Urban Forum

The World Urban Forum (WUF) concluded today with a...

Private sector deemed key to unlocking AfCFTA potential

The private sector’s role is vital to fully unlock...

As India, Africa Get Closer, Critical Minerals Hold Key

Second, financing mechanisms must be reimagined. Critical minerals projects...

How Football Supports Ethiopia’s Economic Growth

Football’s Role in Ethiopia’s Growth On match day, football in...

GameZone Tongits Win Like a Pro: Advanced Strategies You Need

What really separates a casual Tongits player from a...

INVITATION TO BID

Sale of Unserviceable Touchscreen Displays and UPS REF#PRO32-3-752-PMU/26-4-1 The United Nations...

Call for Transformative Companies in Digital Economy

Partner with GIZ PSD-E to scale ICT, BPO, or...
spot_img

Related Articles

Popular Categories

spot_imgspot_img