Sunday, August 23, 2026

ብሔራዊ ባንክ በአይኤምኤፍ ምክረ-ሀሳብ መሰረት በውጭ ምንዛሪ ዝውውር ላይ የነበሩ ገደቦችን አላላ

👉 የውጭ ምንዛሪ ሂሳብ ለመክፈት ይቀመጥ የነበረው የ100 ዶላር ቅድመ-ሁኔታ ቀርቷል

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከአለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) ጋር የተደረሰውን ስምምነትና የድርጅቱን የአሰራር ደንብ አንቀጽ 8 ድንጋጌዎችን መሠረት በማድረግ፣ በውጭ ምንዛሪ አሰራር ላይ ተጥለው የነበሩ በርካታ የቁጥጥር ቅድመ-ሁኔታዎችንና ክልከላዎችን በከፍተኛ ሁኔታ ማላላቱን አስታወቀ።

ባንኩ ዛሬ የካቲት 4 ቀን 2018 ዓ.ም. እንደገለፀው ፣ ማሻሻያው ከሐምሌ 2016 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ እየተደረገ ያለውን የተሟላ የማክሮ-ኢኮኖሚ ሪፎርም ይበልጥ ለማጎልበትና የውጭ ምንዛሪ ገበያውን ነፃ፣ ግልጽና ቀልጣፋ ለማድረግ ያለመ ነው።

ይህ እርምጃ ኢትዮጵያ ከአይኤምኤፍ የሽግግር ድንጋጌዎች (አንቀጽ 14) በመውጣት፣ ክፍት የሆነ ዓለም አቀፍ የክፍያ ስርዓትን ወደሚያበረታታው አንቀጽ 8 ለመሸጋገር የምታደርገው ጥረት አካል ነው።

በአዲሱ መመሪያ መሠረት ግለሰቦችና ቤተሰቦች በውጭ ምንዛሪ አጠቃቀም ላይ ሰፊ ነፃነት ተሰጥቷቸዋል። ከዛሬ ጀምሮ ማንኛውም የውጭ ምንዛሪ ሂሳብ ያለው ግለሰብ አስፈላጊውን ሕጋዊ ሰነድ በማቅረብ፤ ለትዳር አጋሩና ለልጆቹ የትምህርት፣ የሕክምና እና የጉዞ ወጪዎችን ካለው የውጭ ምንዛሪ ሂሳብ መክፈል ይችላል።

በተጨማሪም ኢትዮጵያውያን በውጭ ሀገር ለሚኖሩ ዘመዶቻቸው እስከ 3,000 የአሜሪካ ዶላር የሚደርስ የገንዘብ ድጋፍ እንዲልኩ የተፈቀደ ሲሆን፣ ቀደም ሲል የውጭ ምንዛሪ ቁጠባ ሂሳብ ለመክፈት እንደ ቅድመ-ሁኔታ ይቀመጥ የነበረው የ100 ዶላር አነስተኛ ተቀማጭ ሙሉ በሙሉ ቀርቷል።

ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡ ነዋሪዎችም ይዘውት የመጡትን ማንኛውንም የውጭ ምንዛሪ መጠን ያለ ጉምሩክ ሰነድ በባንኮችና በምንዛሪ ቢሮዎች ወደ ብር የመመንዘር ወይም ወደ ውጭ ምንዛሪ ሂሳባቸው የማስገባት መብት ተሰጥቷቸዋል።

የአገልግሎት ዘርፍ ላኪዎችን ለማበረታታት ይረዳ ዘንድ፣ ከሥራቸው የሚያገኙትን የውጭ ምንዛሪ መቶ በመቶ (100%) በሪቴንሽን ሂሳባቸው ውስጥ ያለምንም የጊዜ ገደብ እንዲይዙ ተፈቅዶላቸዋል።

ከዚህ ቀደም ለትርፍ የተቋቋሙ ድርጅቶች ከእርዳታና ከስጦታ የሚያገኙትን የውጭ ምንዛሪ በተለያዩ የሂሳብ አይነቶች (ተንቀሳቃሽ፣ ቁጠባና የጊዜ ገደብ) ማስቀመጥ እንዲችሉ ተደርጓል።

በሌላ በኩል፣ የውጭ ቀጥተኛ ኢንቨስተሮች፣ ኤምባሲዎችና ዓለም አቀፍ ተቋማት ያለ ብሔራዊ ባንክ ፈቃድ በንግድ ባንኮች የውጭ ምንዛሪ ሂሳብ መክፈት የሚችሉ ሲሆን፣ የሀገር ውስጥ ድርጅቶችም ኢንቨስትመንታቸውን በብሔራዊ ባንክ እያስመረመሩ ከሀገር ውጭ መዋእለ ነዋያቸውን ማፍሰስ እንዲችሉ መንገድ ተመቻችቷል።

የባንኮች ሚና እና የቴክኖሎጂ አጠቃቀም
የንግድ ባንኮች ለደንበኞቻቸው የውጭ ሀገር ክፍያና የኤሌክትሮኒክ ግብይትን የሚያቀላጥፍ ዓለም አቀፍ የክፍያ ካርድ እንዲያዘጋጁ ፈቃድ ተሰጥቷል።

ባንኮቹ የፎርዋርድ የውጭ ምንዛሪ ግብይትንም ያለ ብሔራዊ ባንክ ማረጋገጫ ማከናወን እንዲችሉ ስልጣን ተሰጥቷቸዋል።

ይህ ሰፊ የማሻሻያ እርምጃ የሀገሪቱን የውጭ ምንዛሪ ክምችት ለማሳደግ፣ ሕጋዊ የገንዘብ ዝውውርን በማበረታታት ጥቁር ገበያን ለመዋጋትና የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ሥርዓት ከዓለም አቀፍ አሰራር ጋር ለማስማማት ትልቅ ፋይዳ እንደሚኖረው የብሔራዊ ባንክ መግለጫ ያመለክታል።

ይህ እርምጃ ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ በ2024 የገባችውን ቃል ማለትም የተዘበራረቁ (ባለብዙ) የምንዛሬ ተመኖችን የማስቀረት እና ለወቅታዊ ዓለም አቀፍ ግብይቶች የሚፈጸሙ ክፍያዎች ላይ የሚጣሉ ገደቦችን የማንሳት ቁርጠኝነትን በተግባር ያሳየ መሆኑ ተገልጿል። የአይኤምኤፍ የተራዘመ የብድር አገልግሎት ድጋፍም እነዚህን መሰረታዊ የፖሊሲ ለውጦች በቀጥታ የሚያግዝ መሆኑ ይታወቃል።

በኢያሱ ዘካሪያስ

Hot this week

Production up, but the ‘cost’ variable weighs heavily

Production is up in 2021 for the Italian agricultural...

Luminos Fund’s catch-up education programs in Ethiopia recognized

The Luminos Fund has been named a top 10...

Well-planned cities essential for a resilient future in Africa concludes the World Urban Forum

The World Urban Forum (WUF) concluded today with a...

Private sector deemed key to unlocking AfCFTA potential

The private sector’s role is vital to fully unlock...

The FX Auction Meant to Restore Order Turns Two

The foreign-exchange auction turns two this month. Its 25...

Ethiopia dominates Kenya’s informal export market, claims over 50% share

Ethiopia has solidified its position as the premier destination...

Breaking the debt and currency cycle

Ray Dalio’s ‘How Countries Go Broke: The Big Cycle’...

Ethiopia targets China trade gap with export drive 

Ethiopia is stepping up efforts to narrow its widening...

Does the law of attraction really attract wealth?

The promise is irresistible. Think positively, visualise financial success,...

Ebola Cases in Congo Exceed 5,000, Government Data Shows

The number of confirmed Ebola cases in the ​Democratic...

Deadly Attacks on Aid Workers and Contractors Surge in South Sudan as UN Urges Protection

At least 36 humanitarian workers and contractors have been...
spot_img

Related Articles

Popular Categories

spot_imgspot_img