Sunday, August 9, 2026

በአንድ ሳምንት ልዩነት የዶላር ዋጋ ጭማሪ አሳየ፤ ከፍተኛው መግዣ 155.05 ብር ደረሰ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በሕገ-ወጥ የውጭ ምንዛሬ ገበያ ላይ የታየውን የዋጋ መናር ለመቆጣጠር እየወሰደ በሚገኘዉ እርምጃ፣ ዛሬ ጥር 26 ቀን 2018 ዓ.ም. በባንኮች በኩል የሚሸጠው የዶላር ዋጋ 155.05 ብር መድረሱ ታውቋል። ይህ እርምጃ የመጣው በጥቁር ገበያ የዶላር ዋጋ እስከ 190 ብር አሻቅቦ በነበረበት ወቅት ነው።

የዶላር ፍላጎቱ ድንገት የጨመረው በቻይና አዲስ ዓመት ምክንያት ነው። የካቲት ወር ላይ በቻይና ፋብሪካዎችና ወደቦች ሥራ ስለሚያቆሙ፣ ኢትዮጵያውያን አስመጪዎች እስከ ሚያዝያና ግንቦት የሚበቃቸውን ዕቃ አሁኑኑ ለማዘዝ ዶላር ፍለጋ ወደ ገበያው ጎርፈዋል። ይህ ግፊት በጥቁር ገበያው ላይ ትልቅ የዋጋ ንረት ፈጥሮ ነበር።

ይህንን የፍላጎት ግፊት ለመቀነስ ባንኩ ባለፈው ሳምንት (ጥር 19) ሪከርድ የሆነ የ500 ሚሊዮን ዶላር ልዩ ጨረታ በማካሄድ ባንኮች የአስመጪዎችን ፍላጎት እንዲያሟሉ አድርጓል።

በሌላ በኩል ደግሞ ንኮች የብድር ሰነድ (LC) ሲከፍቱ የጉምሩክ ኮሚሽንን የዋጋ መረጃ እንዲጠቀሙ ታዘዋል። ይህም አስመጪዎች ዕቃዎችን ከትክክለኛ ዋጋቸው በታች በማስመዝገብ በሕገ-ወጥ መንገድ ዶላር እንዳያወጡ ይከለክላል።

ዛሬ ማክሰኞ ጥር 26፤2018 ዓ.ም. በተካሄደው 17ኛው ዙር ጨረታ፣ ባንኩ 70 ሚሊዮን ዶላር ለገበያ መቅረብ ይታወቃል። በዛሬዉ ጨረታው የታየው የ155.05 ብር ተመን ከባለፈው ሳምንት የ23 ሳንቲም ጭማሪ አሳይቷል።

በዚህ ጨረታ በባንኮች በኩል የቀረበው የፍላጎት መጠን 127.25 ሚሊዮን ዶላር በመሆኑ፣ አቅርቦቱና ፍላጎቱ ባለመመጣጠኑ ምክንያት በባንኮች መካከል ከፍተኛ ፉክክር ተፈጥሯል።

በዚህም ምክንያት በጨረታው ከተሳተፉ 19 ባንኮች መካከል ዶላር ማግኘት የቻሉት 8 ባንኮች ብቻ ሲሆኑ በጨረታው የቀረበው ዝቅተኛው የመግዣ ዋጋ ደግሞ 154.8141 ብር ሆኖ ተመዝግቧል።

የዘርፉ ባለሙያዎች እንደሚሉት፣ ብሔራዊ ባንክ ባለፉት ሁለት ወራት ብቻ ወደ 890 ሚሊዮን ዶላር ለገበያ ማቅረቡ በጥቁር ገበያና በባንክ መካከል ያለውን ልዩነት እያጠበበው ይሄዳል። የዛሬው ጨረታ ዋጋ መጨመርም፣ ገበያው ወደ ትክክለኛ የዋጋ ግኝት እየሄደ መሆኑን ያሳያል።

ከዚሁ ጋር ተያይዞ አለምአቀፍ የገንዘብ ድርጅት ( አይኤምኤፍ) ከሰሞኑ ባወጣዉ ሪፖርት በባንኮች እና በትይዩ ገበያ (ጥቁር ገበያ) መካከል ያለው የዋጋ ልዩነት በቅርብ ሳምንታት ውስጥ ወደ 13 በመቶ ከፍ ብሏል።

በዚህም ከመስከረም እስከ ጥቅምት አጋማሽ ድረስ ባለው ጊዜ ውስጥ በይፋዊው የባንክ ተመን እና በጥቁር ገበያው መካከል ያለው ልዩነት ከ10 በመቶ በታች ወርዶ የነበረ ቢሆንም፣ አሁን ላይ ግን ልዩነቱ በድጋሚ እያገረሸ መምጣቱን ተመላክቷል።

ለዚህም እንደ ዋና ምክንያት የተቀመጠው፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከፍተኛ መጠን ያለው የውጭ ምንዛሬን ከጨረታ ውጭ ለኢትዮጵያ ንግድ ባንክ መሸጡ ነዉ ያለዉ ድርጅቱ ይህም የምንዛሬ ተመኑ በገበያ ውስጥ ያለውን ትክክለኛ የፍላጎት እና የአቅርቦት ሁኔታ እንዳያንጸባርቅ አድርጎታል።

በተጨማሪም ብሔራዊ ባንክ በሚያካሂደው የውጭ ምንዛሬ ጨረታ ላይ ባንኮች ሊያገኙ የሚችሉት ድርሻ ላይ ገደብ መቀመጡ፣ ባንኮች ያላቸውን የምንዛሬ ፍላጎት በነፃነት እንዳያሟሉ እና ትክክለኛ የዋጋ ግኝት እንዳይኖር እንቅፋት መሆኑን አይኤምኤፍ አስታውቋል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በበኩሉ ገበያ መር የምንዛሬ ሥርዓት ተግባራዊ መደረጉን ተከትሎ፣ እንዲህ ያሉ ጨረታዎችን ማካሄዱ የውጭ ምንዛሬ እጥረትን ለመቅረፍና ለንግድ ባንኮች የጥሬ ገንዘብ እጥረትን ለመፍታት ያለመ እንደሆነ ገልጿል። ባንኩ በቀጣይም በተያዘለት መርሃ ግብር መሠረት የውጭ ምንዛሬ ሽያጩን እንደሚቀጥል አስታውቋል።

በኢያሱ ዘካሪያስ

Hot this week

Production up, but the ‘cost’ variable weighs heavily

Production is up in 2021 for the Italian agricultural...

Luminos Fund’s catch-up education programs in Ethiopia recognized

The Luminos Fund has been named a top 10...

Well-planned cities essential for a resilient future in Africa concludes the World Urban Forum

The World Urban Forum (WUF) concluded today with a...

Private sector deemed key to unlocking AfCFTA potential

The private sector’s role is vital to fully unlock...

Djibouti urged to tighten debt controls

A new economic assessment recommends that Djibouti implement tighter...

Who benefits from the migrant chaos in Spain?

What happened in the North African Spanish enclave of...

Childcare seen as economic infrastructure, not just welfare

Childcare should be treated as a core economic investment...

The Commercialization of Hope

Hope has always occupied a unique place in human...

MPs Warn Insecurity Could Jeopardize Elections

South Sudanese lawmakers warned on Wednesday that worsening insecurity...

Death Row Inmates Desperate to Escape Execution in Saudi Arabia Call the BBC

. ... Other foreigners, including Pakistanis, Sudanese and Jordanians,...

Addis Standard Editor-in-Chief Abducted, Offices Raided, Equipment Seized

JAKENN Publishing PLC, publisher of Addis Standard tri-lingual publications,...

Sudan Army Receives Pakistani Armoured Vehicles and Drones, Military Sources Say

The Sudanese army received Pakistani-made Mohafiz armoured vehicles last...
spot_img

Related Articles

Popular Categories

spot_imgspot_img