Friday, May 22, 2026

ዮሐንስ አያሌው (ዶ/ር) የፀደይ ባንክ ፕሬዝዳንት ለመሆን ከስምምነት መድረሳቸው ተገለጸ

የአማራ ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ በመሆን ሲያገለግሉ የቆዩት ዮሐንስ አያሌው (ዶ/ር)፣ በቅርቡ የፕሬዝዳንት ለውጥ ባደረገው ፀደይ ባንክ ውስጥ አቶ መኮንን የለውምወሰንን ተክተው ለመሥራት ከስምምነት ላይ መድረሳቸው ካፒታል ጋዜጣ ከምንጮቹ ተሰምቷል።

ዮሐንስ ቀደም ሲል በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ምክትል ገዥነትና ዋና ኢኮኖሚስት እንዲሁም ደግሞ በኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዝዳንትነት ያካበቱትን ሰፊ ልምድ ይዘው ከመስከረም 3 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ የአማራ ባንክን ሲመሩ የቆዩ ቢሆንም፣ አሁን ግን ወደ ፀደይ ባንክ ለመዘዋወር መወሰናቸው ታውቋል።

ይህንን ተከትሎም አማራ ባንክ ባዶ የሆነውን የዋና ሥራ አስፈጻሚ ቦታ ለመሙላት ብቁ የሆኑ አመራሮችን ለማግኘት ፍለጋ ላይ መሆኑን የውስጥ የካፒታል ምንጮች ጠቁመዋል።

የቀድሞው አማራ ብድርና ቁጠባ ተቋም ወደ ባንክነት በመሸጋገር ፀደይ ባንክ ተብሎ ከተሰየመ በኋላ፣ ባንኩን በፕሬዝዳንትነት ሲመሩ የቆዩት አቶ መኮንን የለውምወሰን በምን ምክንያት ኃላፊነታቸውን እንደለቀቁ በይፋ አልተገለጸም።

አቶ መኮንን ስራቸውን መልቀቃቸውን ተከትሎ፣ በአማራ ክልል ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ደረሰ ኃይሉ የሚመራው የባንኩ የዳይሬክተሮች ቦርድ ወ/ሮ የሺእመቤት ተፈራን በተጠባባቂ ፕሬዝዳንትነት መመደቡ ይታወሳል። ይሁን እንጂ ባንኩ አሁን ካለበት ከባድ የፋይናንስ ሁኔታ አንጻር ዶ/ር ዮሐንስን በቋሚነት ለመሾም ስምምነት ላይ መደረሱ ተመልክቷል።

ፀደይ ባንክ በቅርቡ ይፋ ባደረገው የ2017 የሒሳብ ዓመት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት መሠረት፣ 2.13 ቢሊዮን ብር የሚጠጋ ከፍተኛ ኪሳራ ማጋጠሙን አስታውቋል።

ይህ ከፍተኛ የፋይናንስ ክፍተት ባጋጠመበት ወቅት ዶ/ር ዮሐንስ ወደ አመራርነት መምጣታቸው፣ ባንኩን ከኪሳራ ለማውጣትና ወደ ትርፋማነት ለመመለስ ካለው ከፍተኛ ተስፋ የመነጨ እንደሆነ ይገመታል።

Hot this week

Production up, but the ‘cost’ variable weighs heavily

Production is up in 2021 for the Italian agricultural...

Luminos Fund’s catch-up education programs in Ethiopia recognized

The Luminos Fund has been named a top 10...

Well-planned cities essential for a resilient future in Africa concludes the World Urban Forum

The World Urban Forum (WUF) concluded today with a...

Private sector deemed key to unlocking AfCFTA potential

The private sector’s role is vital to fully unlock...

India’s Africa policy needs sustained engagement, not periodic summits

One of the persistent weaknesses of the India-Africa Forum...

Fall in Love with Impact, Not Your Organization”: The Development Sector’s Toughest Lesson

The Mastercard Foundation, a Canadian organization, celebrated its 20th...

University of Gondar, Mastercard Foundation scholars advance disability inclusion

A decade-long partnership between the University of Gondar, Queen’s...

Name: Tamiru Moges

2. Education:    Marketing Management (BA Degree) 3. Company name: B-Creative Marketing...

“Country Ownership Begins with Women’s Leadership”

In Ethiopia’s ongoing effort to strengthen its health system,...
spot_img

Related Articles

Popular Categories

spot_imgspot_img