Monday, August 31, 2026

ዮሐንስ አያሌው (ዶ/ር) የፀደይ ባንክ ፕሬዝዳንት ለመሆን ከስምምነት መድረሳቸው ተገለጸ

የአማራ ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ በመሆን ሲያገለግሉ የቆዩት ዮሐንስ አያሌው (ዶ/ር)፣ በቅርቡ የፕሬዝዳንት ለውጥ ባደረገው ፀደይ ባንክ ውስጥ አቶ መኮንን የለውምወሰንን ተክተው ለመሥራት ከስምምነት ላይ መድረሳቸው ካፒታል ጋዜጣ ከምንጮቹ ተሰምቷል።

ዮሐንስ ቀደም ሲል በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ምክትል ገዥነትና ዋና ኢኮኖሚስት እንዲሁም ደግሞ በኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዝዳንትነት ያካበቱትን ሰፊ ልምድ ይዘው ከመስከረም 3 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ የአማራ ባንክን ሲመሩ የቆዩ ቢሆንም፣ አሁን ግን ወደ ፀደይ ባንክ ለመዘዋወር መወሰናቸው ታውቋል።

ይህንን ተከትሎም አማራ ባንክ ባዶ የሆነውን የዋና ሥራ አስፈጻሚ ቦታ ለመሙላት ብቁ የሆኑ አመራሮችን ለማግኘት ፍለጋ ላይ መሆኑን የውስጥ የካፒታል ምንጮች ጠቁመዋል።

የቀድሞው አማራ ብድርና ቁጠባ ተቋም ወደ ባንክነት በመሸጋገር ፀደይ ባንክ ተብሎ ከተሰየመ በኋላ፣ ባንኩን በፕሬዝዳንትነት ሲመሩ የቆዩት አቶ መኮንን የለውምወሰን በምን ምክንያት ኃላፊነታቸውን እንደለቀቁ በይፋ አልተገለጸም።

አቶ መኮንን ስራቸውን መልቀቃቸውን ተከትሎ፣ በአማራ ክልል ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ደረሰ ኃይሉ የሚመራው የባንኩ የዳይሬክተሮች ቦርድ ወ/ሮ የሺእመቤት ተፈራን በተጠባባቂ ፕሬዝዳንትነት መመደቡ ይታወሳል። ይሁን እንጂ ባንኩ አሁን ካለበት ከባድ የፋይናንስ ሁኔታ አንጻር ዶ/ር ዮሐንስን በቋሚነት ለመሾም ስምምነት ላይ መደረሱ ተመልክቷል።

ፀደይ ባንክ በቅርቡ ይፋ ባደረገው የ2017 የሒሳብ ዓመት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት መሠረት፣ 2.13 ቢሊዮን ብር የሚጠጋ ከፍተኛ ኪሳራ ማጋጠሙን አስታውቋል።

ይህ ከፍተኛ የፋይናንስ ክፍተት ባጋጠመበት ወቅት ዶ/ር ዮሐንስ ወደ አመራርነት መምጣታቸው፣ ባንኩን ከኪሳራ ለማውጣትና ወደ ትርፋማነት ለመመለስ ካለው ከፍተኛ ተስፋ የመነጨ እንደሆነ ይገመታል።

Hot this week

Production up, but the ‘cost’ variable weighs heavily

Production is up in 2021 for the Italian agricultural...

Luminos Fund’s catch-up education programs in Ethiopia recognized

The Luminos Fund has been named a top 10...

Well-planned cities essential for a resilient future in Africa concludes the World Urban Forum

The World Urban Forum (WUF) concluded today with a...

Private sector deemed key to unlocking AfCFTA potential

The private sector’s role is vital to fully unlock...

EPSS wins gold award at Fifth Africa Supply Chain Excellence Awards

The Ethiopian Pharmaceutical Supply Service (EPSS) has won the...

REQUEST FOR EXPRESSION OF INTEREST (EOI)

This notice is placed by UNECA. The accuracy, reliability...

REQUEST FOR EXPRESSION OF INTEREST (EOI)

This notice is placed by UNECA. The accuracy, reliability...

INVITATION FOR OPEN BID

National Bank of Ethiopia invites interested and eligible bidders...

INITIATIVE AFRICA (IA)CALL FOR CONSULTANCY SERVICES

Baseline Study ConsultantCSIF II Consortium-Wide Baseline Study Initiative Africa (IA),...

Advertisement Open for LOCAL Procurement

Topic- UNICEF (Ethiopia) wishes to request eligible bidders to...

Tender Notice

The Office of the United Nations High Commissioner for...

Regional implementation failures turn new compensation proclamation into new bottleneck

Ethiopian Electric Power (EEP) has revealed that ongoing and...
spot_img

Related Articles

Popular Categories

spot_imgspot_img