Monday, November 10, 2025

በኢትዮጵያ የሚገኙ ሱዳናውያን በጦርነትና በገቢ እጦት መካከል 300 ዶላር ቅጣት እየተጠየቁ ነው

ተባለበኢትዮጵያ የሚገኙ በጦርነት የተፈናቀሉ ሱዳናውያን፣ ከሰብዓዊ እና ከኑሮ ፈተናዎች በተጨማሪ፣ የመኖሪያ ፈቃድ እና የቪዛ እድሳት ጋር ተያይዘው ከባድ የገንዘብ ጫና እየደረሰባቸው መሆኑን ተገልጿል።

የቅርብ ጊዜ መረጃዎች እንደሚያሳዩት ግጭቱ ከጀመረ ወዲህ ኢትዮጵያ ከ100 ሺህ በላይ ሱዳናውያንን ተቀብላለች። ዜጎቹ እንደሚሉት፣ ባለሥልጣናት ለእያንዳንዱ ወርሃዊ ቪዛ እድሳት 100 ዶላር ክፍያ የሚጠይቁ ሲሆን፣ እድሳቱን በማዘግየት ለእያንዳንዱ ወር ደግሞ 300 ዶላር ቅጣት ይጥላሉ።

የሱዳን ትሪቢዩን ዘገባ እንደሚያሳየው፣ ወርሃዊ የመግቢያ ቪዛዎችን ማደስ በጦርነት፣ በገቢ መጥፋት እና በሀብት እጥረት መካከል እጅግ በጣም አድካሚና ውድ ሂደት ሆኗል።

በተለይም ጦርነቱ በቀጠለበት በዚህ ወቅት፣ ይህ የገንዘብ ክፍያና ቅጣት ከሱዳናውያን ስቃይ ጋር የሚጣጣም ባለመሆኑ፣ የሰብዓዊ ውሳኔ እንዲሰጥና ጣልቃ ገብነት እንዲደረግ ጥሪ ቀርቧል።

ሱዳናውያኑ አክለውም፣ ቪዛ የማራዘም ሂደት ላይ ካለው ከፍተኛ ክፍያና ቅጣት በተጨማሪ፣ በአዲስ አበባ የሚገኘው የሱዳን ኤምባሲ ለችግሮቻቸው ተገቢ ምላሽ እየሰጠ አለመሆኑን ተችተዋል። ዘገባዉ ፤ ዜጎቹ ኤምባሲው ለከፍተኛ ችግሮች፣ ለምሳሌም ለምግብ እና ለመድሃኒት እጥረት፣ ምላሽ እንደማይሰጥ እና ሰራተኞቹም በአካል ተገኝተው የዜጎችን ሁኔታ ክትትል እንደማያደርጉ አስረድቷል።

ሱዳናውያኑ፣ ቀደም ሲል እንደተደረገው፣ የኢትዮጵያ መንግስት ጣልቃ በመግባት ለሱዳናውያን የስደተኞችን ሁኔታ ከግምት ውስጥ ያስገባ የዘጠኝ ወር የቪዛ ነፃ ፈቃድ እንዲሰጥላቸው ጠይቀዋል።

Hot this week

Production up, but the ‘cost’ variable weighs heavily

Production is up in 2021 for the Italian agricultural...

Luminos Fund’s catch-up education programs in Ethiopia recognized

The Luminos Fund has been named a top 10...

Well-planned cities essential for a resilient future in Africa concludes the World Urban Forum

The World Urban Forum (WUF) concluded today with a...

Private sector deemed key to unlocking AfCFTA potential

The private sector’s role is vital to fully unlock...

የፈረንሳዩ ካርፉር የኢትዮጵያን ገበያ ለመቀላቀል የመሰማሪያ ሞዴል ማዘጋጀቱን አስታወቀ

የዓለማችን ግዙፍ የጅምላና ችርቻሮ ንግድ ኩባንያ ካርፉር በቅርቡ ወደ...

Cotton Village Ethiopia: Pioneering Regenerative Cotton for Sustainable Growth

The Cotton Village Initiative (CVI), also known as Cotton...

Debt restructuring, currency challenges highlighted in IMF’s review

An International Monetary Fund (IMF) delegation is currently in...

COMESA court of justice rules in favor of Ethiopian lawyer, invalidates judge appointment

In a landmark ruling with significant ramifications, the Common...

Ethiopia implements customs tariff reductions with 24 AfCFTA Member States to boost continental trade

Ethiopia has officially commenced implementing customs duty reductions with...
spot_img

Related Articles

Popular Categories

spot_imgspot_img