Thursday, February 5, 2026

በኢትዮጵያ የሚገኙ ሱዳናውያን በጦርነትና በገቢ እጦት መካከል 300 ዶላር ቅጣት እየተጠየቁ ነው

ተባለበኢትዮጵያ የሚገኙ በጦርነት የተፈናቀሉ ሱዳናውያን፣ ከሰብዓዊ እና ከኑሮ ፈተናዎች በተጨማሪ፣ የመኖሪያ ፈቃድ እና የቪዛ እድሳት ጋር ተያይዘው ከባድ የገንዘብ ጫና እየደረሰባቸው መሆኑን ተገልጿል።

የቅርብ ጊዜ መረጃዎች እንደሚያሳዩት ግጭቱ ከጀመረ ወዲህ ኢትዮጵያ ከ100 ሺህ በላይ ሱዳናውያንን ተቀብላለች። ዜጎቹ እንደሚሉት፣ ባለሥልጣናት ለእያንዳንዱ ወርሃዊ ቪዛ እድሳት 100 ዶላር ክፍያ የሚጠይቁ ሲሆን፣ እድሳቱን በማዘግየት ለእያንዳንዱ ወር ደግሞ 300 ዶላር ቅጣት ይጥላሉ።

የሱዳን ትሪቢዩን ዘገባ እንደሚያሳየው፣ ወርሃዊ የመግቢያ ቪዛዎችን ማደስ በጦርነት፣ በገቢ መጥፋት እና በሀብት እጥረት መካከል እጅግ በጣም አድካሚና ውድ ሂደት ሆኗል።

በተለይም ጦርነቱ በቀጠለበት በዚህ ወቅት፣ ይህ የገንዘብ ክፍያና ቅጣት ከሱዳናውያን ስቃይ ጋር የሚጣጣም ባለመሆኑ፣ የሰብዓዊ ውሳኔ እንዲሰጥና ጣልቃ ገብነት እንዲደረግ ጥሪ ቀርቧል።

ሱዳናውያኑ አክለውም፣ ቪዛ የማራዘም ሂደት ላይ ካለው ከፍተኛ ክፍያና ቅጣት በተጨማሪ፣ በአዲስ አበባ የሚገኘው የሱዳን ኤምባሲ ለችግሮቻቸው ተገቢ ምላሽ እየሰጠ አለመሆኑን ተችተዋል። ዘገባዉ ፤ ዜጎቹ ኤምባሲው ለከፍተኛ ችግሮች፣ ለምሳሌም ለምግብ እና ለመድሃኒት እጥረት፣ ምላሽ እንደማይሰጥ እና ሰራተኞቹም በአካል ተገኝተው የዜጎችን ሁኔታ ክትትል እንደማያደርጉ አስረድቷል።

ሱዳናውያኑ፣ ቀደም ሲል እንደተደረገው፣ የኢትዮጵያ መንግስት ጣልቃ በመግባት ለሱዳናውያን የስደተኞችን ሁኔታ ከግምት ውስጥ ያስገባ የዘጠኝ ወር የቪዛ ነፃ ፈቃድ እንዲሰጥላቸው ጠይቀዋል።

Hot this week

Production up, but the ‘cost’ variable weighs heavily

Production is up in 2021 for the Italian agricultural...

Luminos Fund’s catch-up education programs in Ethiopia recognized

The Luminos Fund has been named a top 10...

Well-planned cities essential for a resilient future in Africa concludes the World Urban Forum

The World Urban Forum (WUF) concluded today with a...

Private sector deemed key to unlocking AfCFTA potential

The private sector’s role is vital to fully unlock...

ዮሐንስ አያሌው (ዶ/ር) የፀደይ ባንክ ፕሬዝዳንት ለመሆን ከስምምነት መድረሳቸው ተገለጸ

የአማራ ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ በመሆን ሲያገለግሉ የቆዩት ዮሐንስ...

በአንድ ሳምንት ልዩነት የዶላር ዋጋ ጭማሪ አሳየ፤ ከፍተኛው መግዣ 155.05 ብር ደረሰ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በሕገ-ወጥ የውጭ ምንዛሬ ገበያ ላይ የታየውን...

መንግሥት በነዳጅ ላይ ሲያደርግ የነበረውን ድጎማ እስከ መጪው የካቲት ወር ሙሉ በሙሉ ሊያነሳ ነው

መንግሥት ላለፉት አራት ዓመታት በነዳጅ ምርቶች ላይ ሲያደርግ የነበረውን...

Six African cities take stock of fiscal reforms in drive toward sustainable urban finance

City leaders and finance officials from across the continent...

KOICA strengthens WFP’s efforts to prevent malnutrition in Ethiopia

The United Nations World Food Programme (WFP) has welcomed a...
spot_img

Related Articles

Popular Categories

spot_imgspot_img