Thursday, February 5, 2026

ገቢዎች ሚኒስቴር ከ50 ሺህ ብር በላይ ግብይት ላይ የተሰጠውን የቫት ማቀናነስ ማብራሪያ ‘ለጊዜው ተፈጻሚ አይደረግ’ አለ

ገቢዎች ሚኒስቴር ከ50 ሺህ ብር በላይ በሆነ ጥሬ ገንዘብ የሚፈጸሙ የንግድ ግብይቶችን በተመለከተ የገንዘብ ሚኒስቴር ከሰሞኑ የሰጠውን ማብራሪያ በከፊል አግደ። በተለይም የተጨማሪ እሴት ታክስ (ቫት) ማቀናነስ/ተመላሽ ጉዳይ ላይ የተሰጠው ማብራሪያ “ለጊዜው ተፈጻሚ እንዳይደረግ” የሚል መመሪያ አስተላልፏል።

የገንዘብ ሚኒስቴር በጥቅምት 27 ቀን 2018 ዓ.ም. ማብራሪያው፣ በገቢ ግብር ማሻሻያ አዋጅ ቁጥር 1395/2017 የተቀመጠው ከ50 ሺህ ብር በላይ የጥሬ ገንዘብ ግብይት ገደብ ተፈፃሚ የሚሆነው ለገቢ ግብር ብቻ መሆኑንና የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) የግብዓት ታክስ የማቀናነስ መብትን እንደማይገድብ በዝርዝር አስቀምጦ ነበር።

በተጨማሪም፣ ገዥዎች ከገደቡ በላይ በጥሬ ገንዘብ ከከፈሉ፣ ትርፍ ግብር በሚሰላበት ጊዜ ትርፍ ክፍያው እንደተቀናሽ ወጪ እንደማይያዝ እንዲሁም ሻጮችም ከገደቡ በላይ ጥሬ ገንዘብ ከተቀበሉ እኩል የገንዘብ ቅጣት እንደሚጠብቃቸው አስታውቆ እንደነበር ይታወሳል።ሆኖም የገቢዎች ሚኒስቴር በጥቅምት 29 ቀን 2018 ዓ.ም. ባስተላለፈው የሰርኩላር ደብዳቤ ፤ የገንዘብ ሚኒስቴር የሰጠው የቫት ማቀናነስ ማብራሪያ አዋጁ የተፈለገበትን “የታክስ ስወራ ድርጊት ለማስቀረት” የሚለውን ዓላማ “በአግባቡ ያልተመለከተ” በመሆኑ ውይይት እንዲደረግበት በመግለፅ  ” የቫት ማቀናነስ/ተመላሽ ጉዳይ ለጊዜው ተፈጻሚ እንዳይደረግ አዟል።

በገቢ ግብር አዋጁ ላይ የተቀመጡት ሌሎች የጥሬ ገንዘብ ገደቦች፣ በተለይም ገዥዎች የተቀናሽ ወጪ መብታቸውን የሚያጡበት እና ሻጮች ቅጣት የሚጣልባቸው ድንጋጌዎች፣ ተግባራዊ እንደሚሆኑ ሚኒስትሩ አስታውቋል።በተጨማሪም፣ የገቢዎች ሚኒስቴር ገቢ ወይም ሽያጭ የለንም በማለት ባዶ የሚያሳውቁ ታክስ ከፋዮችን አነስተኛ አማራጭ ግብር ለማስከፈል የሚያስችል ዝርዝር ማብራሪያ ከገንዘብ ሚኒስቴር እስኪመጣ ድረስ፣ ቀደም ሲል በተሰጠው አሰራር እንዲስተናገዱ ማዘዙን ለካፒታል የደረሰው የአፈፃፀም መመሪያው ያመለክታል።

Hot this week

Production up, but the ‘cost’ variable weighs heavily

Production is up in 2021 for the Italian agricultural...

Luminos Fund’s catch-up education programs in Ethiopia recognized

The Luminos Fund has been named a top 10...

Well-planned cities essential for a resilient future in Africa concludes the World Urban Forum

The World Urban Forum (WUF) concluded today with a...

Private sector deemed key to unlocking AfCFTA potential

The private sector’s role is vital to fully unlock...

ዮሐንስ አያሌው (ዶ/ር) የፀደይ ባንክ ፕሬዝዳንት ለመሆን ከስምምነት መድረሳቸው ተገለጸ

የአማራ ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ በመሆን ሲያገለግሉ የቆዩት ዮሐንስ...

በአንድ ሳምንት ልዩነት የዶላር ዋጋ ጭማሪ አሳየ፤ ከፍተኛው መግዣ 155.05 ብር ደረሰ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በሕገ-ወጥ የውጭ ምንዛሬ ገበያ ላይ የታየውን...

መንግሥት በነዳጅ ላይ ሲያደርግ የነበረውን ድጎማ እስከ መጪው የካቲት ወር ሙሉ በሙሉ ሊያነሳ ነው

መንግሥት ላለፉት አራት ዓመታት በነዳጅ ምርቶች ላይ ሲያደርግ የነበረውን...

Six African cities take stock of fiscal reforms in drive toward sustainable urban finance

City leaders and finance officials from across the continent...

KOICA strengthens WFP’s efforts to prevent malnutrition in Ethiopia

The United Nations World Food Programme (WFP) has welcomed a...
spot_img

Related Articles

Popular Categories

spot_imgspot_img