Saturday, April 11, 2026

ገቢዎች ሚኒስቴር ከ50 ሺህ ብር በላይ ግብይት ላይ የተሰጠውን የቫት ማቀናነስ ማብራሪያ ‘ለጊዜው ተፈጻሚ አይደረግ’ አለ

ገቢዎች ሚኒስቴር ከ50 ሺህ ብር በላይ በሆነ ጥሬ ገንዘብ የሚፈጸሙ የንግድ ግብይቶችን በተመለከተ የገንዘብ ሚኒስቴር ከሰሞኑ የሰጠውን ማብራሪያ በከፊል አግደ። በተለይም የተጨማሪ እሴት ታክስ (ቫት) ማቀናነስ/ተመላሽ ጉዳይ ላይ የተሰጠው ማብራሪያ “ለጊዜው ተፈጻሚ እንዳይደረግ” የሚል መመሪያ አስተላልፏል።

የገንዘብ ሚኒስቴር በጥቅምት 27 ቀን 2018 ዓ.ም. ማብራሪያው፣ በገቢ ግብር ማሻሻያ አዋጅ ቁጥር 1395/2017 የተቀመጠው ከ50 ሺህ ብር በላይ የጥሬ ገንዘብ ግብይት ገደብ ተፈፃሚ የሚሆነው ለገቢ ግብር ብቻ መሆኑንና የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) የግብዓት ታክስ የማቀናነስ መብትን እንደማይገድብ በዝርዝር አስቀምጦ ነበር።

በተጨማሪም፣ ገዥዎች ከገደቡ በላይ በጥሬ ገንዘብ ከከፈሉ፣ ትርፍ ግብር በሚሰላበት ጊዜ ትርፍ ክፍያው እንደተቀናሽ ወጪ እንደማይያዝ እንዲሁም ሻጮችም ከገደቡ በላይ ጥሬ ገንዘብ ከተቀበሉ እኩል የገንዘብ ቅጣት እንደሚጠብቃቸው አስታውቆ እንደነበር ይታወሳል።ሆኖም የገቢዎች ሚኒስቴር በጥቅምት 29 ቀን 2018 ዓ.ም. ባስተላለፈው የሰርኩላር ደብዳቤ ፤ የገንዘብ ሚኒስቴር የሰጠው የቫት ማቀናነስ ማብራሪያ አዋጁ የተፈለገበትን “የታክስ ስወራ ድርጊት ለማስቀረት” የሚለውን ዓላማ “በአግባቡ ያልተመለከተ” በመሆኑ ውይይት እንዲደረግበት በመግለፅ  ” የቫት ማቀናነስ/ተመላሽ ጉዳይ ለጊዜው ተፈጻሚ እንዳይደረግ አዟል።

በገቢ ግብር አዋጁ ላይ የተቀመጡት ሌሎች የጥሬ ገንዘብ ገደቦች፣ በተለይም ገዥዎች የተቀናሽ ወጪ መብታቸውን የሚያጡበት እና ሻጮች ቅጣት የሚጣልባቸው ድንጋጌዎች፣ ተግባራዊ እንደሚሆኑ ሚኒስትሩ አስታውቋል።በተጨማሪም፣ የገቢዎች ሚኒስቴር ገቢ ወይም ሽያጭ የለንም በማለት ባዶ የሚያሳውቁ ታክስ ከፋዮችን አነስተኛ አማራጭ ግብር ለማስከፈል የሚያስችል ዝርዝር ማብራሪያ ከገንዘብ ሚኒስቴር እስኪመጣ ድረስ፣ ቀደም ሲል በተሰጠው አሰራር እንዲስተናገዱ ማዘዙን ለካፒታል የደረሰው የአፈፃፀም መመሪያው ያመለክታል።

Hot this week

Production up, but the ‘cost’ variable weighs heavily

Production is up in 2021 for the Italian agricultural...

Luminos Fund’s catch-up education programs in Ethiopia recognized

The Luminos Fund has been named a top 10...

Well-planned cities essential for a resilient future in Africa concludes the World Urban Forum

The World Urban Forum (WUF) concluded today with a...

Private sector deemed key to unlocking AfCFTA potential

The private sector’s role is vital to fully unlock...

#Sponsored በኢትዮጵያ የዲጂታል ክፍያ ፣ ብሔራዊ ባንክ የአገልግሎት ገንዘብ ላይ ተጽዕኖ

በ2026 ዲጂታል ክፍያ በኢትዮጵያ ለማንኛውም ንግድ ጠቃሚ ነው። ኩባንያዎች...

Djibouti votes in high-stakes presidential election

Citizens of Djibouti headed to the polls on Friday...

Wegagen Bank partners with IFC on $10 million trade finance guarantee

Wegagen Bank has signed a strategic partnership with the...

Djibouti presidential campaign concludes peacefully ahead of Friday vote

This morning, the Campaign Director for the Union for...

Incumbent President Ismail Omar Guelleh concludes campaign with grand rally in Djibouti City

Incumbent President and presidential candidate Ismail Omar Guelleh held...

EDR deploys Gondola Wagons to ease fuel shortage-driven cargo backlog

The Ethio-Djibouti Railway (EDR), a bilateral venture owned by...

Djibouti’s largest port facility reports sufficient cargo handling capacity

Despite a growing number of cargo vessels being rerouted...

Birr devaluation pushes fertilizer, fuel costs higher as wheat output rises

Ethiopia’s sharp currency depreciation is driving up fertilizer and...
spot_img

Related Articles

Popular Categories

spot_imgspot_img