Thursday, February 5, 2026

ፍርድ ቤቱ በኢትዮጵያና በአዲስ አበባ ንግድ ምክር ቤቶች ሕንፃ ውዝግብ ላይ የእግድ ውሳኔ አስተላለፈ

በኢትዮጵያ ንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት (ኢትዮጵያ ቻምበር) እና በአዲስ አበባ የንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት (አዲስ ቻምበር) መካከል በሜክሲኮ አደባባይ በሚገኘው የንግድ ምክር ቤቶች ሕንፃ ላይ በቀረበው የይገባኛል ውዝግብ ላይ፣ የቂርቆስ ምድብ 1ኛ ፍ/ብሄር ችሎት የእግድ ዉሳኔ አስተላልፏል።

ፍርድ ቤቱ በዛሬው እለት በሰጠው ውሳኔ መሰረት፣ ኢትዮጵያ ቻምበር ቀደም ሲል ይዞ የነበረውን የቢሮ ክፍል በአስቸኳይ ለአዲስ ቻምበር እንዲያስረክብ ጥብቅ ትዕዛዝ ሰጥቷል።

ፍርድ ቤቱ ይህን ውሳኔ የሰጠው፣ ኢትዮጵያ ቻምበር ቀደም ሲል የፍርድ ቤቱን ብይን በመጣስ፣ አዲስ ቻምበር ይዟቸው የነበሩ ክፍሎችን በኃይል እንደያዘ አዲስ ቻምበር ባቀረበው አቤቱታ መሰረት ነው።

ፍርድ ቤቱ ህዳር 1 ቀን 2018 ዓ.ም. ባሳለፈው ብይን፣ ተከሳሽ (ኢትዮጵያ ቻምበር) ሕንጻውን ለልማት ከማዋሉ በፊት ለአዲስ ቻምበር ምትክ ክፍሎችን አስቀድሞ ማዘጋጀትና ለፍርድ ቤቱ ማሳወቅ እንደነበረበት አመልክቶ ነበር።

የኢትዮጵያ ቻምበር ይህንን ትዕዛዝ በመጣስ የክፍሎቹን ቁልፎች ሰብሮ መግባቱ በአዲስ ቻምበር በኩል መገለጹን ተከትሎ፣ ፍርድ ቤቱ ኢትዮጵያ ቻምበር ክፍሎቹን በአስቸኳይ ለከሳሽ (አዲስ ቻምበር) እንዲያስረክብ በድጋሚ በጥብቅ አዟል።

የካፒታል ዘገባ የዓይን እማኞችን ዋቢ አድርጎ እንደዘገበው፣ ቁጥራቸው 20 ገደማ የሆኑ የኢትዮጵያ ቻምበር ሰራተኞች የቢሮውን ግድግዳና በር በመስበር ንብረቶችን ወደ ውጪ ሲጥሉ ነበር።

የኢትዮጵያ ንግድና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ሰብስብ አባፊራ በበኩላቸው፣ “በፍርድ ቤቱ ተጥሎ የነበረውን የማልማት እግድ ትላንት (ህዳር 1 ቀን 2018 ዓ.ም.) በማንሳቱ ነው ዛሬ (ህዳር 2 ቀን 2018) ወደ ተግባር የገባነው” ሲሉ ለካፒታል ገልፀው ነበር። የንግድ ምክር ቤቶች ሕንፃ ውዝግብ ወደ አዲስ ምዕራፍ መሸጋገሩን የፍርድ ቤቱ ውሳኔ ያመለክታል።

Hot this week

Production up, but the ‘cost’ variable weighs heavily

Production is up in 2021 for the Italian agricultural...

Luminos Fund’s catch-up education programs in Ethiopia recognized

The Luminos Fund has been named a top 10...

Well-planned cities essential for a resilient future in Africa concludes the World Urban Forum

The World Urban Forum (WUF) concluded today with a...

Private sector deemed key to unlocking AfCFTA potential

The private sector’s role is vital to fully unlock...

ዮሐንስ አያሌው (ዶ/ር) የፀደይ ባንክ ፕሬዝዳንት ለመሆን ከስምምነት መድረሳቸው ተገለጸ

የአማራ ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ በመሆን ሲያገለግሉ የቆዩት ዮሐንስ...

በአንድ ሳምንት ልዩነት የዶላር ዋጋ ጭማሪ አሳየ፤ ከፍተኛው መግዣ 155.05 ብር ደረሰ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በሕገ-ወጥ የውጭ ምንዛሬ ገበያ ላይ የታየውን...

መንግሥት በነዳጅ ላይ ሲያደርግ የነበረውን ድጎማ እስከ መጪው የካቲት ወር ሙሉ በሙሉ ሊያነሳ ነው

መንግሥት ላለፉት አራት ዓመታት በነዳጅ ምርቶች ላይ ሲያደርግ የነበረውን...

Six African cities take stock of fiscal reforms in drive toward sustainable urban finance

City leaders and finance officials from across the continent...

KOICA strengthens WFP’s efforts to prevent malnutrition in Ethiopia

The United Nations World Food Programme (WFP) has welcomed a...
spot_img

Related Articles

Popular Categories

spot_imgspot_img