Sunday, March 1, 2026

ፒተር ንዴግዋን የተኩት ኤርሚያስ እሸቱ የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ቦርድን ሊመሩ ነው

ሳፋሪኮም ቴሌኮሙኒኬሽንስ ኢትዮጵያ ኃ.የተ.የግ.ማ.፣ የኩባንያውን የአድቫይዘሪ ቦርድ ሊቀመንበርነት ቦታ ለአዲስ መሪ መስጠቱን አስታውቋል። የግሎባል ፓርትነርሺፕ ፎር ኢትዮጵያ (GPE) ቦርድ አቶ ኤርሚያስ እሸቱን ቀደም ሲል የቦርዱን ሊቀመንበርነት ሲመሩ የነበሩትን ፒተር ንዴግዋን በመተካት፣ ከህዳር 1 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የአድቫይዘሪ ቦርድ ሊቀመንበር አድርጎ ሾሟል።

ይህ ሹመት ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ለአካባቢያዊ አመራር (localization) እና ለኢትዮጵያውያን በከፍተኛ የአመራር ሚናዎች ውስጥ ተሳትፎ እንዲኖራቸው ለሚያደርገው ጥረት ትልቅ ምዕራፍ እንደሆነ ተገልጿል።

አቶ ኤርሚያስ ከመጋቢት 12 ቀን 2017 ዓ.ም. ጀምሮ የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የአድቫይዘሪ ቦርድን የተቀላቀሉ የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ አባል ነበሩ። አሁን ወደ ሊቀመንበርነት ማደጋቸው የኩባንያው በአገር ውስጥ አመራር ላይ ያለውን እምነት ያጎላል ተብሏል።

በአዲሱ ኃላፊነታቸውም ቦርዱ ውጤታማ ሆኖ እንዲሠራ መምራትና ማስተባበር፣ እንዲሁም ኩባንያውን በውጭ ግንኙነት መወከል ይጠበቅባቸዋል።

የGPE ቦርድ ሊቀመንበር እና የሳፋሪኮም ኃ.የተ.የግ.ማ. ዋና ስራ አስፈጻሚ የሆኑት ፒተር ንዴግዋ በሰጡት አስተያየት፡- “የእርሳቸው (የኤርሚያስ) በፋይናንስ፣ በአስተዳደር እና በተቋማዊ ለውጥ ላይ ያለው ሰፊ ልምድ፣ ከገበያው ጥልቅ ግንዛቤ ጋር ተዳምሮ ኩባንያውን ወደ ቀጣዩ የዕድገት ምዕራፍ ለመምራት ያስችላቸዋል።” ብለዋል

ፒተር ንዴግዋ ከመጋቢት 2017 ዓ.ም. ጀምሮ የግሎባል ፓርትነርሺፕ ፎር ኢትዮጵያ ቦርድ እና የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የአድቫይዘሪ ቦርድ ሊቀመንበር ሆነው ሲያገለግሉ የቆዩ ሲሆን፣ አሁን ግን በGPE ቦርድ ሊቀመንበርነት ብቻ ይቀጥላሉ።

GPE ቦርድ ብሪቲሽ ኢንተርናሽናል ኢንቨስትመንት፣ ኢንተርናሽናል ፋይናንስ ኮርፖሬሽን፣ ቮዳኮም፣ ቮዳፎን፣ ሳፋሪኮም ኃ.የተ.የግ.ማ. እና ሱሚቶሞ ኮርፖሬሽን የተሰኙ ዓለም አቀፍ ተቋማትን ያካትታል።

አቶ ኤርሚያስ እሸቱ የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ዘመናዊነት እና የግል ዘርፍ ዕድገት በማስፋፋት የሚታወቁ፣ በንግድ አስተዳደር፣ በፋይናንስ እና በቴክኖሎጂ ዘርፎች ከ25 ዓመታት በላይ ልምድ ያካበቱ መሪ መሆናቸው ተመላክቷል።

ቀደም ሲል የኢትዮጵያ ምርት ገበያ (ECX) ዋና ስራ አስፈጻሚ በመሆን የኢትዮጵያን የመጀመሪያውን የኤሌክትሮኒክስ ግብይት መድረክ የጀመሩ ሲሆን፣ ዘመን ባንክን ከመሰረቱት እና በኋላም ሊቀመንበር ከሆኑት መካከል አንዱ ናቸው።

በአቶ ኤርሚያስ አመራር ስር የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ቦርድ ህግ አስተዳደርን በማጠናከር፣ የስራ ዕድል በመፍጠር እና ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የድርጅት አሰራርን በመትከል በኢትዮጵያ አሳታፊ ዲጂታል-ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ለማምጣት ትኩረት እንደሚያደርግ ተጠቁሟል።

Hot this week

Production up, but the ‘cost’ variable weighs heavily

Production is up in 2021 for the Italian agricultural...

Luminos Fund’s catch-up education programs in Ethiopia recognized

The Luminos Fund has been named a top 10...

Well-planned cities essential for a resilient future in Africa concludes the World Urban Forum

The World Urban Forum (WUF) concluded today with a...

Private sector deemed key to unlocking AfCFTA potential

The private sector’s role is vital to fully unlock...

Over 71 Billion Birr in Shared Revenue Transferred to Ethiopia’s Regions in Seven Months

The Speaker of the House of Federation, Agegnehu Teshager,...

Israeli President Hails Ethiopia as Key African Partner Following High-Level Talks

President Isaac Herzog affirmed that Ethiopia remains an exceptionally...

Prime Minister Abiy Confers with President Ilham Aliyev of Azerbaijan

Prime Minister Abiy Ahmed held talks with President Ilham...

Ethiopian Customs Commission Fully Digitalized

The Ethiopian Customs Commission (ECC) has fully digitalized its...

Federation of Saudi Chambers Announces the Formation of the Saudi-Ethiopian Business Council

The Federation of Saudi Chambers announced the formation of...

Interdealer Market

An interdealer market is a specialized trading platform where...

IATA Opens Nominations for 2026 Edition of Diversity & Inclusion Awards

The International Air Transport Association (IATA) announced the opening...
spot_img

Related Articles

Popular Categories

spot_imgspot_img