Thursday, December 11, 2025

አይኤምኤፍ ለኢትዮጵያ 261 ሚሊዮን ዶላር እንዲለቀቅ የባለሞያዎች ደረጃ ስምምነት ላይ ደረሰ

ዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (አይኤምኤፍ) ከኢትዮጵያ ጋር በ3.4 ቢሊዮን ዶላር የተራዘመ የብድር ፋሲሊቲ መርሃግብር በአራተኛው ግምገማ ላይ በባለሞያዎች ደረጃ ስምምነት ላይ መድረሱን አስታውቋል።

ይህ ስምምነት የአይኤምኤፍ ሥራ አስፈፃሚ ቦርድ ሲያጸድቀው፣ ቀጣዩ የ261 ሚሊዮን ዶላር ክፍያ ለኢትዮጵያ እንዲለቀቅ መንገድ ይከፍታል። ይህ ክፍያ ሲፈጸም በአጠቃላይ በፕሮግራሙ ስር ለኢትዮጵያ የተሰጠው የገንዘብ ድጋፍ ወደ 2.13 ቢሊዮን ዶላር ከፍ ይላል።

የገንዘብ ተቋሙ ባወጣው መግለጫ፣ የኢትዮጵያ መንግሥት የጀመረውን የማክሮ ኢኮኖሚ ማረጋጋት እና የልማት ማሻሻያዎችን በመገምገም፣ “የተሃድሶውን ፍጥነት ማስቀጠል የማክሮ ኢኮኖሚ መረጋጋትን ለማጠናከር እና በመካከለኛ ጊዜ ዕድገትንና ድህነትን ለመቀነስ ቁልፍ ይሆናል” የሚል አስተያየት ሰጥቷል።

ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ በሐምሌ 2024 የድጋፍ ብድሩን ስትይዝ፣ ከባድ የውጭ ዕዳ መልሶ የማዋቀር ሥራ ላይ ትገኛለች። አይኤምኤፍ ባወጣው ሪፖርት፣ በG20 የጋራ ማዕቀፍ ስር የዕዳ ዘላቂነትን ለመመለስ የሚደረጉ ጥረቶች እየገፉ መሆናቸውን ጠቁሟል።

ምንም እንኳን ኢትዮጵያ ከሁለትዮሽ አበዳሪዎች ጋር በመደበኛ ዕዳዋ ላይ ስምምነት ላይ ብትደርስም፣ ባለሀብቶች ከ1 ቢሊዮን ዶላር የዩሮቦንድ ጋር በተያያዘ በሚደረገው የዕዳ ቅናሽ መጠን ላይ አለመግባባት መኖሩ የሂደቱን መጓተት እንዳስከተለ ይታወቃል።

በአይኤምኤፍ የባለሞያዎች ቡድን መሪ በሆኑት በአልቫሮ ፒሪስ የሚመራው ቡድን ከጥቅምት 20 እስከ ህዳር 4 ቀን 2018 ዓ.ም. ድረስ በአዲስ አበባ በመገኘት፣ በአይኤምኤፍ የተራዘመ የብድር ፋሲሊቲ መርሃግብር ስር በአራተኛው ግምገማ ዙሪያ ውይይት ማድረጋቸው ይታወቃል። ይህ ተከትሎ ደግሞ ከህዳር 24 እስከ 26 ቀን 2018 ዓ.ም. የቀጠለው ዉይይት በአዲስ አበባ ተካሄዶ ነበር።

ሚስተር ፒሪስ እንደተናገሩት ፤ ​“የአይኤምኤፍ ባለሞያዎች ቡድን እና የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት በተራዘመ የብድር ፋሲሊቲ ስምምነት ስር በኢትዮጵያ ኢኮኖሚያዊ ፕሮግራም በአራተኛው ግምገማ ላይ በባለሞያዎች ደረጃ ስምምነት ላይ ደርሰዋል። ስምምነቱ በሚቀጥሉት ሳምንታት የአይኤምኤፍ ማኔጅመንት እና ሥራ አስፈፃሚ ቦርድ ማጽደቅ ይጠበቅበታል።

የማሻሻያውን ፍጥነት ማስቀጠል የማክሮ ኢኮኖሚ መረጋጋትን ለማጠናከር እና በመካከለኛ ጊዜ ዕድገትንና ድህነትን ለመቀነስ ቁልፍ ይሆናል ያሉት አልቫሮ የዋጋ ግሽበትን ለመግታት ጥብቅ የገንዘብ ፖሊሲ መከተል ተገቢ እንደሆነ አፅንኦ ሰጥተዉ ተናግረዋል ።

የባለሞያዎች ቡድን ከአስተዳዳሪዎች ጋር ባለፈዉ ሳምንት በኢትዮጵያ በነበራቸዉ ቆይታ ከገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሽዴ፣ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ እዮብ ተካለኝ እና ሌሎች ከፍተኛ ባለሥልጣናት ጋር ተገናኝቶ ውይይት ማድረጋቸው ይታወሳል።

Hot this week

Production up, but the ‘cost’ variable weighs heavily

Production is up in 2021 for the Italian agricultural...

Luminos Fund’s catch-up education programs in Ethiopia recognized

The Luminos Fund has been named a top 10...

Well-planned cities essential for a resilient future in Africa concludes the World Urban Forum

The World Urban Forum (WUF) concluded today with a...

Private sector deemed key to unlocking AfCFTA potential

The private sector’s role is vital to fully unlock...

ሁሉም ባንኮች አዲስ እና ነባር ሂሳቦችን ለማስተሳሰር ወደ VeriFayda 2 እንዲሸጋገሩ ተወሰነ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እና የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም፣ የፋይዳ ዲጂታል...

NBE orders financial institutions to link accounts with Fayda ID

The National Bank of Ethiopia (NBE) has ordered all...

TECNO’s AFCON-Ready AI Features Reflect a New Era in Mobile Sports Viewing

#Advertorial TECNO, official CAF global partner, introduces four intelligent tools...

Instant Payments, Big Data & High Availability: Why Banks in Ethiopia Need a Robust Data Backbone

By Demos Kyriacou Instant payments, big data and high availability...

Notice of Meeting

To All Shareholders of Shabelle Bank S.C Shabelle Bank Share...

Invitation to Bid for

Long Term Agreement for 24+24 months for Procurement of...

Invitation to Bid for

Long Term Agreement for 24+24 months for Procurement of...

UNHCR Representation in Ethiopia

Tel:+251 11 6612822          P. O. Box 1076                                                               ...
spot_img

Related Articles

Popular Categories

spot_imgspot_img