Thursday, February 5, 2026

ምክር ቤቱ ከ55 ዓመታት በኋላ የተሻሻለውን የዕፅዋት ጥበቃና ኳራንታይን አዋጅ አጸደቀ

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባኤ፤ ለግማሽ ክፍለ ዘመን ያህል ሲሰራበት የቆየውንና ኋላ ቀር የሆነውን የእፅዋት ጥበቃና ኳራንታይን አዋጅ የሚያሻሽል አዲስ ረቂቅ አዋጅ በሙሉ ድምፅ አፅድቋል።

ይህ አዲስ የጸደቀው አዋጅ ቁጥር 1400/2018 ሆኖ የሚመዘገብ ሲሆን፣ ዋነኛ ዓላማውም የሥነ ሕይወት ዕፅዋት ብልሽትንና ብክነትን መከላከል እንዲሁም ዘመናዊ የተባይ መከላከልና መቆጣጠር ሥርዓትን መዘርጋት ነው።

የዕፅዋት ጥበቃና ኳራንታይን አዋጅ ከ55 ዓመታት በፊት ወደ ሥራ የገባ በመሆኑ ለወቅታዊ ቁጥጥር አመቺ ባለመሆኑ መሻሻሉ የግድ መሆኑ ተገልጿል።

በምክር ቤቱ የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ባቀረበው ሪፖርት ላይ ሰፊ ውይይት የተደረገ ሲሆን፣ በአዲሱ አዋጅ መሠረት በዕፅዋት ላይ ጉዳት ያደረሰ ማንኛውም አካል ከ1 እስከ 5 ዓመት በሚደርስ እስራት እንዲቀጣ ተደንግጓል።

በተጨማሪም ተቆጣጣሪ አካላት የሕግ ጥሰት ሲፈፅሙ ወይም የጉቦ ተግባር ላይ ሲሰማሩ በቀጥታ በእስራት እንዲቀጡ መደረጉ ተገልጿል።

የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ አቶ ሰለሞን ላሌ እንደገለጹት፤ አዋጁ ደረጃውን የጠበቀ የተባይ አሰሳና ቅኝት ለማድረግ እንዲሁም ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የሀገሪቱን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ጉልህ ድርሻ ይኖረዋል።

Hot this week

Production up, but the ‘cost’ variable weighs heavily

Production is up in 2021 for the Italian agricultural...

Luminos Fund’s catch-up education programs in Ethiopia recognized

The Luminos Fund has been named a top 10...

Well-planned cities essential for a resilient future in Africa concludes the World Urban Forum

The World Urban Forum (WUF) concluded today with a...

Private sector deemed key to unlocking AfCFTA potential

The private sector’s role is vital to fully unlock...

ዮሐንስ አያሌው (ዶ/ር) የፀደይ ባንክ ፕሬዝዳንት ለመሆን ከስምምነት መድረሳቸው ተገለጸ

የአማራ ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ በመሆን ሲያገለግሉ የቆዩት ዮሐንስ...

በአንድ ሳምንት ልዩነት የዶላር ዋጋ ጭማሪ አሳየ፤ ከፍተኛው መግዣ 155.05 ብር ደረሰ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በሕገ-ወጥ የውጭ ምንዛሬ ገበያ ላይ የታየውን...

መንግሥት በነዳጅ ላይ ሲያደርግ የነበረውን ድጎማ እስከ መጪው የካቲት ወር ሙሉ በሙሉ ሊያነሳ ነው

መንግሥት ላለፉት አራት ዓመታት በነዳጅ ምርቶች ላይ ሲያደርግ የነበረውን...

Six African cities take stock of fiscal reforms in drive toward sustainable urban finance

City leaders and finance officials from across the continent...

KOICA strengthens WFP’s efforts to prevent malnutrition in Ethiopia

The United Nations World Food Programme (WFP) has welcomed a...
spot_img

Related Articles

Popular Categories

spot_imgspot_img