Wednesday, May 13, 2026

አይ.ኤፍ.ሲ በኢትዮጵያ ለሚከናወኑ የሸራተን ሆቴል ፕሮጀክቶች የ80 ሚሊዮን ዶላር ብድር ለመስጠት እቅድ መያዙ ተነገረ

የዓለም ባንክ የግል ዘርፍ አበዳሪ የሆነው ኢንተርናሽናል ፋይናንስ ኮርፖሬሽን ፣ በኢትዮጵያ የቱሪዝም እና የኢንቨስትመንት ዘርፍን ለማነቃቃት ለሚድሮክ ኢትዮጵያ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር እስከ 80 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ( በግምት ወደ 12.4 ቢሊዮን ብር ) የሚደርስ የብድር ኢንቨስትመንት ለማቅረብ ማቀዱን ይፋ አደረገ።

ተቋሙ ያቀረበው የብድር ድጋፍ  ዓላማውም በሀገሪቱ ታዋቂ የሆነውንና ለረጅም ዓመታት አገልግሎት ሲሰጥ የቆየውን ሸራተን አዲስ ሆቴልን በከፍተኛ ደረጃ ለማደስና አዲስ በሸራተን ስም የሚጠራ ተጨማሪ ሆቴል ለመገንባት ነው።

እንደ አይ.ኤፍ.ሲ ከሆነ ፣ አጠቃላይ የፕሮጀክቱ ወጪ 116 ሚሊዮን ዶላር እንደሚሆን ተገምቷል። ከዚህ ውስጥ ተቋሙ ለማቅረብ ያሰበው 80 ሚሊዮን ዶላር ሲሆን፣ ቀሪው ወጪ በባለሀብቱ እንደሚሸፈን ይጠበቃል።

ይህ ግዙፍ ኢንቨስትመንት ሁለት ዋና ዋና ክፍሎች እንዳሉት የተገለፀ ሲሆን የመጀመሪያዉ በአፍሪካ ደረጃ ቀዳሚ ከሚባሉ የቅንጦት ሆቴሎች አንዱ የሆነውንና ለአህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ጉባኤዎች ማዕከል ሆኖ የሚያገለግለውን ሸራተን አዲስን ዘመናዊና ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ እድሳት ማድረግ።

ሌላኛዉ ደግሞ በአዲስ አበባ ከተማ የሸራተን ብራንድ ተደራሽነትን ይበልጥ የሚያሰፋ አዲስ የሆቴል ግንባታ ማከናወን የሚሉት ይገኙበታል።

የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በታዋቂው ዓለም አቀፍ ባለሀብት ሼክ መሐመድ ሁሴን አሊ አል-አሙዲ እና በወይዘሮ ሶፊያ ሳላህ አል-አሙዲ ባለቤትነት የሚመራ ነው።

ይህ የኢንቨስትመንት ዕቅድ በአሁኑ ወቅት በዝግጅት ላይ ያለ ሲሆን፣ የአይ.ኤፍ.ሲ የዳይሬክተሮች ቦርድ የፊታችን የካቲት 21 ቀን 2018 ዓ.ም በሚያደርገው ስብሰባ የብድር ጥያቄውን መርምሮ የመጨረሻ ውሳኔ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል።

ታሪካዊው ዋቢ ሸበሌ ሆቴል በትላንትናው ዕለት ጥር 13 ቀን 2018 ዓ.ም. ከቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ወራሾች ወደ ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ መዘዋወሩን ተከትሎ፣ ሆቴሉ በዓለም አቀፉ የማሪዮት ደረጃ ዘመናዊና ቅንጡ ሆኖ እንዲታደስ መታቀዱ ተመላክቷል።

ኢትዮጵያ 32ኛውን የዓለም የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤ (COP32) ለማዘጋጀት መመረጧን ተከትሎ፣ ሚድሮክ ሆቴሉን ለጉባኤው ተሳታፊዎች ምቹና ከፍተኛ ደረጃ ያለው ለማድረግ በልዩ ትኩረት እየሰራ መሆኑ መግለፁ ይታወሳል።

ሚድሮክ በአፍሪካ፣ በአውሮፓ፣ በመካከለኛው ምስራቅና በዩናይትድ ስቴትስ ሰፊ የንግድ መረብ ያለው ሲሆን፣ በኢትዮጵያም በግብርና፣ በማኑፋክቸሪንግ፣ በማዕድን፣ በሪል እስቴት፣ በሆቴል፣ በኮንስትራክሽንና በፋይናንስ ዘርፎች በንቃት በመሳተፍ የሀገሪቱን ኢኮኖሚ በማንቀሳቀስ ረገድ ጉልህ ድርሻ እንዳለው መረጃዎች ያመለክታሉ።

Hot this week

Production up, but the ‘cost’ variable weighs heavily

Production is up in 2021 for the Italian agricultural...

Luminos Fund’s catch-up education programs in Ethiopia recognized

The Luminos Fund has been named a top 10...

Well-planned cities essential for a resilient future in Africa concludes the World Urban Forum

The World Urban Forum (WUF) concluded today with a...

Private sector deemed key to unlocking AfCFTA potential

The private sector’s role is vital to fully unlock...

ETHIOPIA’S EXPANDING DIGITAL ECONOMY: TRENDS AND OPPORTUNITIES.

The digital landscape in Ethiopia has slowly grown over...

Ethiopia defers Eurobond payment to next fiscal year

The Ethiopian government has officially announced the deferral of...

The Digital Engine Behind Ethiopia’s Infrastructure and Construction Renaissance

As Ethiopia marks Infrastructure and Construction Week 2026, the...

New UN report urges accelerated forest action before 2030

At the start of this year’s UN Forum on Forests,...

Senior officials among 13 charged in alleged multi-million-birr fuel diversion

Thirteen individuals, including senior officials in Ethiopia’s petroleum sector,...
spot_img

Related Articles

Popular Categories

spot_imgspot_img