Friday, June 5, 2026

አላይድ ጎልድ በመጪዉ ሚያዚያ ወር በኢትዮጵያ የወርቅ ምርት ሊጀምር መሆኑ ተገለጸ

የካናዳው “አላይድ ጎልድ” ኩባንያ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኘው የኩርሙክ የወርቅ ማዕድን ፕሮጀክት በመጪው ሚያዝያ ወር ስራ እንደሚጀምር አስታወቀ። ኩባንያው ፕሮጀክቱ በ2026 ሶስተኛ ሩብ ዓመት ውስጥ ሙሉ በሙሉ ወደ ምርት እንደሚሸጋገር የገለጸ ሲሆን፣ በየዓመቱ 290 ሺህ አውንስ ወርቅ ለማምረት አቅዷል።

የኩባንያው ዋና ስራ አስፈጻሚ ፒተር ማሮን እንደገለጹት፣ ኩባንያው ለፍለጋ ስራ በየዓመቱ 8 ሚሊዮን ዶላር የመደበ ሲሆን፣ በቀጣይ አምስት ዓመታት ውስጥ የወርቅ ክምችቱን ወደ 5 ሚሊዮን አውንስ ለማሳደግ እየሰራ ይገኛል።

ማዕድን ማውጫው ከሰፈራ መንደሮች ርቆ የሚገኝ በመሆኑ ምንም ዓይነት የህዝብ ማፈናቀል ስራ እንዳልተከናወነ የጠቀሱት ስራ አስፈጻሚው፣ ድርጅታቸው የአካባቢውን ነዋሪዎች በቅድሚያ ለመቅጠር ፖሊሲ ቀርጾ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ገልጸዋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ ኩባንያው በኢትዮጵያ ምርት ሊጀምር መሆኑን ተከትሎ የአክሲዮን ዋጋው ባለፈው አንድ ዓመት ውስጥ በአራት እጥፍ በማደግ ከፍተኛ ውጤት አስመዝግቧል።

አላይድ ጎልድ ከኢትዮጵያ በተጨማሪ በማሊ እና በኮትዲቯር ግዙፍ የወርቅ ማዕድን ማውጫዎች እንዳሉት ይታወቃል።

Hot this week

Production up, but the ‘cost’ variable weighs heavily

Production is up in 2021 for the Italian agricultural...

Luminos Fund’s catch-up education programs in Ethiopia recognized

The Luminos Fund has been named a top 10...

Well-planned cities essential for a resilient future in Africa concludes the World Urban Forum

The World Urban Forum (WUF) concluded today with a...

Private sector deemed key to unlocking AfCFTA potential

The private sector’s role is vital to fully unlock...

iibGroup Expands Chevening Partnership to Ethiopia as Part of Broader Regional Engagement

Building on its successful partnership with the Chevening Scholarships...

EthSwitch records 1 million daily EthioPay-IPS transactions, wins African financial inclusion award

EthSwitch, Ethiopia’s national payment switch, has recorded more than...

IGAD Urges Urgent Overhaul of Crowded Polling Stations to Meet International Standards

Following the conclusion of Ethiopia’s 7th General Election, the...
spot_img

Related Articles

Popular Categories

spot_imgspot_img