Sunday, May 10, 2026

የዩሮ ቦንድ የዕዳ ሽግሽግ ስምምነቱ ከአበዳሪዎች ኮሚቴ መመሪያ ጋር ባለመጣጣሙ እንዲቆም ተወሰነ

የገንዘብ ሚኒስቴር የሀገሪቱን የ1 ቢሊዮን ዶላር የዩሮ ቦንድ ዕዳ ለማዋቀር ከግል አበዳሪዎች ኮሚቴ ጋር ደርሶት የነበረውን የመርህ ስምምነት ተግባራዊ እንደማያደርግ በይፋ አስታወቀ።

ጥር 2 ቀን 2026 ዓ.ም የተደረሰው ይህ ስምምነት እንዲቆም የተወሰነው፣ የመንግስታት አበዳሪዎች ኮሚቴ እና ዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት ስምምነቱን መርምረው ካጠናቀቁ በኋላ ነው።

የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ አሰንደገለፁት፤ የስምምነቱ መቋረጥ ዋነኛው ምክንያት “የአበዳሪዎች የእኩልነት መርህ”  ካለመከበሩ ጋር የተያያዘ ነው። የመንግስታት አበዳሪዎች ኮሚቴስምምነቱ ከሌሎች ይፋዊ አበዳሪዎች ጋር ከተደረገው የዕዳ ሽግሽግ ማዕቀፍ ጋር እንደማይጣጣም ለኢትዮጵያ መንግስት በደብዳቤ አሳውቋል።

ይህንን ስምምነት ባለበት ሁኔታ ተግባራዊ ማድረግ ሀገሪቱ በሐምሌ ወር 2025 ዓ.ም ከአበዳሪዎች ኮሚቴ ጋር ከፈረመችው የመግባቢያ ሰነድ ጋር የሚቃረን ሆኖ ተገኝቷል።

በተጨማሪም፣ የተደረሰው ስምምነት ኢትዮጵያ ከዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት ጋር ከገባችው የኢኮኖሚ ማሻሻያ መርሃ-ግብር ግቦች እና መለኪያዎች ጋር እንደማይጣጣም ተመልክቷል።

ሚኒስቴሩ እንዳለው ከሆነ፣ ስምምነቱን መቀጠል በሀገሪቱ የማክሮ ኢኮኖሚ መረጋጋት እና በተመዘገቡ የኢኮኖሚ እድገቶች ላይ ከፍተኛ ስጋት ሊፈጥር ስለሚችል በድጋሚ መደራደር የግድ ሆኗል።

በዚህም መሠረት፣ የኢትዮጵያ መንግስት የዕዳ ሽግሽጉን የፋይናንስ ይዘት በተመለከተ ከግል አበዳሪዎች ኮሚቴ ጋር አዲስ ድርድር ለመጀመር መወሰኑን አስታውቋል።

መንግስት ውይይቱን በድጋሚ መክፈት አስፈላጊ ቢሆንም፣ በሁሉም አበዳሪዎች መካከል ፍትሃዊ የዕዳ ጫና ክፍፍልን የሚያረጋግጥ እና የሀገሪቱን የኢኮኖሚ አቅም ያገናዘበ ዘላቂ መፍትሄ ለማምጣት በቁርጠኝነት እንደሚሰራ ገልጿል።

Hot this week

Production up, but the ‘cost’ variable weighs heavily

Production is up in 2021 for the Italian agricultural...

Luminos Fund’s catch-up education programs in Ethiopia recognized

The Luminos Fund has been named a top 10...

Well-planned cities essential for a resilient future in Africa concludes the World Urban Forum

The World Urban Forum (WUF) concluded today with a...

Private sector deemed key to unlocking AfCFTA potential

The private sector’s role is vital to fully unlock...

New UN report urges accelerated forest action before 2030

At the start of this year’s UN Forum on Forests,...

Senior officials among 13 charged in alleged multi-million-birr fuel diversion

Thirteen individuals, including senior officials in Ethiopia’s petroleum sector,...

Sudan and Ethiopia inching closer to war

On Monday, drones struck Khartoum’s international airport, the first...

Türkiye COP31 Presidency declares resilient cities as key priority for Antalya UN Climate Summit

COP31 President-Designate, H.E. Murat Kurum today outlined how Türkiye’s...

United Nations proposes new global dashboard to measure progress beyond GDP

The UN Secretary-General’s Independent High-Level Expert Group on Beyond...
spot_img

Related Articles

Popular Categories

spot_imgspot_img