Wednesday, September 16, 2026

የዩሮ ቦንድ የዕዳ ሽግሽግ ስምምነቱ ከአበዳሪዎች ኮሚቴ መመሪያ ጋር ባለመጣጣሙ እንዲቆም ተወሰነ

የገንዘብ ሚኒስቴር የሀገሪቱን የ1 ቢሊዮን ዶላር የዩሮ ቦንድ ዕዳ ለማዋቀር ከግል አበዳሪዎች ኮሚቴ ጋር ደርሶት የነበረውን የመርህ ስምምነት ተግባራዊ እንደማያደርግ በይፋ አስታወቀ።

ጥር 2 ቀን 2026 ዓ.ም የተደረሰው ይህ ስምምነት እንዲቆም የተወሰነው፣ የመንግስታት አበዳሪዎች ኮሚቴ እና ዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት ስምምነቱን መርምረው ካጠናቀቁ በኋላ ነው።

የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ አሰንደገለፁት፤ የስምምነቱ መቋረጥ ዋነኛው ምክንያት “የአበዳሪዎች የእኩልነት መርህ”  ካለመከበሩ ጋር የተያያዘ ነው። የመንግስታት አበዳሪዎች ኮሚቴስምምነቱ ከሌሎች ይፋዊ አበዳሪዎች ጋር ከተደረገው የዕዳ ሽግሽግ ማዕቀፍ ጋር እንደማይጣጣም ለኢትዮጵያ መንግስት በደብዳቤ አሳውቋል።

ይህንን ስምምነት ባለበት ሁኔታ ተግባራዊ ማድረግ ሀገሪቱ በሐምሌ ወር 2025 ዓ.ም ከአበዳሪዎች ኮሚቴ ጋር ከፈረመችው የመግባቢያ ሰነድ ጋር የሚቃረን ሆኖ ተገኝቷል።

በተጨማሪም፣ የተደረሰው ስምምነት ኢትዮጵያ ከዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት ጋር ከገባችው የኢኮኖሚ ማሻሻያ መርሃ-ግብር ግቦች እና መለኪያዎች ጋር እንደማይጣጣም ተመልክቷል።

ሚኒስቴሩ እንዳለው ከሆነ፣ ስምምነቱን መቀጠል በሀገሪቱ የማክሮ ኢኮኖሚ መረጋጋት እና በተመዘገቡ የኢኮኖሚ እድገቶች ላይ ከፍተኛ ስጋት ሊፈጥር ስለሚችል በድጋሚ መደራደር የግድ ሆኗል።

በዚህም መሠረት፣ የኢትዮጵያ መንግስት የዕዳ ሽግሽጉን የፋይናንስ ይዘት በተመለከተ ከግል አበዳሪዎች ኮሚቴ ጋር አዲስ ድርድር ለመጀመር መወሰኑን አስታውቋል።

መንግስት ውይይቱን በድጋሚ መክፈት አስፈላጊ ቢሆንም፣ በሁሉም አበዳሪዎች መካከል ፍትሃዊ የዕዳ ጫና ክፍፍልን የሚያረጋግጥ እና የሀገሪቱን የኢኮኖሚ አቅም ያገናዘበ ዘላቂ መፍትሄ ለማምጣት በቁርጠኝነት እንደሚሰራ ገልጿል።

Hot this week

Production up, but the ‘cost’ variable weighs heavily

Production is up in 2021 for the Italian agricultural...

Luminos Fund’s catch-up education programs in Ethiopia recognized

The Luminos Fund has been named a top 10...

Well-planned cities essential for a resilient future in Africa concludes the World Urban Forum

The World Urban Forum (WUF) concluded today with a...

Private sector deemed key to unlocking AfCFTA potential

The private sector’s role is vital to fully unlock...

Ethiopia, Kenya finalize preparations to scale up cross-border power trade by December 2026

Ethiopia is finalizing preparations to double its electricity supply...

Ethiopia records 824% remittance growth over the decade, accounting for 5% of national GDP

Ethiopia has rapidly ascended to become Africa’s fourth-largest remittance...

Ethiopia Rejects Commercial Buyback Offer for Looted 18th-Century Royal Gospel

The Ethiopian Heritage Authority has confirmed to Capital that...

Djibouti positions itself as Horn of Africa logistics gateway with new WFP base handover

The Government of Djibouti has officially assumed full management...

Dangote Refinery launches historic $1.6B IPO

The Nigerian Exchange (NGX) officially launched the initial public...

IOM warns Sudan humanitarian system faces collapse within weeks without new funding

The International Organization for Migration (IOM) has issued an...

Safaricom surpasses 15 million subscribers as it marks five years

Safaricom is marking five years since it received a...

Africa’s economic momentum is building as savings and cross-border trade activity accelerate

Rising savings, increasing cross-border payment activity and growing participation...
spot_img

Related Articles

Popular Categories

spot_imgspot_img