Thursday, February 5, 2026

የፈረንሳዩ ካርፉር የኢትዮጵያን ገበያ ለመቀላቀል የመሰማሪያ ሞዴል ማዘጋጀቱን አስታወቀ

የዓለማችን ግዙፍ የጅምላና ችርቻሮ ንግድ ኩባንያ ካርፉር በቅርቡ ወደ ኢትዮጵያ ገበያ ለመግባት የሚያስችለውን የቢዝነስ ሞዴል በማዘጋጀት ላይ መሆኑን ገለጸ።

የካርፉር ኮሜርሻል ዳይሬክተር የሆኑት ጄሮሜ ቦንዚ፣ ኢትዮጵያ ውስጥ ለመሰማራት የሚያስችል የቢዝነስ ሞዴል እየተዘጋጀ መሆኑን ገልጸው፣ ይህን ዕቅድ ወደ ተግባር ለመለወጥ የሚያስችል ቡድን በቅርብ ጊዜ ወደ ኢትዮጵያ እንደሚመጣ አስታውቀዋል።

ይህ የተገለጸው የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ዘለቀ ተመስገን ከኩባንያው ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ጋር ባደረጉት ውይይት ነው።

በውይይቱ ላይ ኮሚሽኑ ኢትዮጵያ ለውጭ ባለሀብቶች ክፍት ባደረገቻቸው አዳዲስ የኢንቨስትመንት ዘርፎችና ያሉ አማራጮችን አስረድተዋል የተባለ ሲሆን ድርጅቱ በበኩሉ ደግሞ የኢትዮጵያን ገበያ ለረጅም ጊዜ ሲከታተለው እንደነበርና ፣ መንግስት የውጪና ገቢ ንግድ ሴክተሩን ለውጭ ባለሀብቶች መክፈቱ ምቹ አጋጣሚ እንደፈጠረላቸው አስረድቷል።

በፈረንጆቹ በ1959 በፈረንሳይ የተመሰረተው ካርፉር በአውሮፓ፣ በእስያ፣ በአፍሪካ እና በላቲን አሜሪካ በሚገኙ መሸጫ ማዕከላቱ በየቀኑ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ደንበኞችን የሚያስተናግድ ዓለም አቀፍ ድርጅት ነው።

Hot this week

Production up, but the ‘cost’ variable weighs heavily

Production is up in 2021 for the Italian agricultural...

Luminos Fund’s catch-up education programs in Ethiopia recognized

The Luminos Fund has been named a top 10...

Well-planned cities essential for a resilient future in Africa concludes the World Urban Forum

The World Urban Forum (WUF) concluded today with a...

Private sector deemed key to unlocking AfCFTA potential

The private sector’s role is vital to fully unlock...

ዮሐንስ አያሌው (ዶ/ር) የፀደይ ባንክ ፕሬዝዳንት ለመሆን ከስምምነት መድረሳቸው ተገለጸ

የአማራ ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ በመሆን ሲያገለግሉ የቆዩት ዮሐንስ...

በአንድ ሳምንት ልዩነት የዶላር ዋጋ ጭማሪ አሳየ፤ ከፍተኛው መግዣ 155.05 ብር ደረሰ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በሕገ-ወጥ የውጭ ምንዛሬ ገበያ ላይ የታየውን...

መንግሥት በነዳጅ ላይ ሲያደርግ የነበረውን ድጎማ እስከ መጪው የካቲት ወር ሙሉ በሙሉ ሊያነሳ ነው

መንግሥት ላለፉት አራት ዓመታት በነዳጅ ምርቶች ላይ ሲያደርግ የነበረውን...

Six African cities take stock of fiscal reforms in drive toward sustainable urban finance

City leaders and finance officials from across the continent...

KOICA strengthens WFP’s efforts to prevent malnutrition in Ethiopia

The United Nations World Food Programme (WFP) has welcomed a...
spot_img

Related Articles

Popular Categories

spot_imgspot_img