Wednesday, April 1, 2026

ደቡብ ሱዳን በ2026 የአፍሪካ ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት እንደምታስመዘግብ ተተነበየ

የአፍሪካ ደሀና በጦርነት ክፉኛ የተጎዳችው ደቡብ ሱዳን፣ እ.ኤ.አ በ2026 የነዳጅ ምርት ወደ ቀድሞ ሁኔታው በመመለሱ ምክንያት በአህጉሪቱ ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት የሚያስመዘግቡ አገራትን እንደምትመራ የዓለም ባንክ አስታወቀ።

የዓለም ባንክ ባወጣው የቅርብ ጊዜው የዓለም የኢኮኖሚ ዕድገት ትንበያ መሠረት፣ የአገሪቱ አጠቃላይ የአገር ውስጥ ምርት (GDP) በ2026 በ48.8 በመቶ ያድጋል ተብሎ ይጠበቃል።

ይህ ከፍተኛ ዕድገት የታቀደው አገሪቱ ባለፈው ዓመት ካጋጠማት የ23.8 በመቶ የኢኮኖሚ ማሽቆልቆል በኋላ መሆኑም ታውቋል።

ከፍተኛ የኢኮኖሚ ማገገም የተገኘው በሁለት ዋና ዋና ምክንያቶች እንደሆነ ሪፖርቱ ያመላክታል። የመጀመሪያው በሱዳን በኩል የሚያልፈው የነዳጅ ማስተላለፊያ ቧንቧ በመጠገኑ የነዳጅ ምርት ወደ መደበኛ ሁኔታው መመለሱ ሲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ ከአምስት ዓመታት የኢኮኖሚ ውድቀት በኋላ በአገሪቱ ውስጥ ያለው የንግድና የኢኮኖሚ እንቅስቃሴዎች መረጋጋት ነው።

ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) በበኩሉ ደቡብ ሱዳን በተጠናቀቀዉ በ2025 በ27.2 በመቶ ዕድገት እንደምታሳይ በመተንበይ የዓለም ባንክን የብሩህ ተስፋ ትንበያ አረጋግጧል። የአገሪቱ መንግሥት ገቢ ከ90 በመቶ በላይ የሚመነጨው ነዳጅ ሽያጭ እንደመሆኑ፣ የቧንቧው ጥገና ለኢኮኖሚው ትልቅ ትንፋሽ ሆኗል።

ሪፖርቱ በ2026 ሌሎች የአፍሪካ አገራት ሊያስመዘግቡት የሚችሉትን ዕድገትም ይፋ አድርጓል። በዚህም መሠረት ጊኒ በ9.3 በመቶ፣ ሩዋንዳ በ7.2 በመቶ፣ ኢትዮጵያ በ7.1 በመቶ እንዲሁም ናይጄሪያ ባለፉት አሥር ዓመታት ያላየችውን ከፍተኛ ዕድገት እንደሚያስመዘግቡ ተተንብዮአል።

በተቃራኒው እንደ ደቡብ አፍሪካ ያሉ ትልልቅ ኢኮኖሚዎች የ1.4 በመቶ ዝቅተኛ ዕድገት እንደሚያሳዩ ተጠቁሟል።

Hot this week

Production up, but the ‘cost’ variable weighs heavily

Production is up in 2021 for the Italian agricultural...

Luminos Fund’s catch-up education programs in Ethiopia recognized

The Luminos Fund has been named a top 10...

Well-planned cities essential for a resilient future in Africa concludes the World Urban Forum

The World Urban Forum (WUF) concluded today with a...

Private sector deemed key to unlocking AfCFTA potential

The private sector’s role is vital to fully unlock...

Container Shortage Reported Due to Maritime Transport Disruptions

The Ethiopian Maritime Authority (EMA) has announced a shortage...

Ethiopia’s MPC Holds Off on Lifting Credit Cap, Citing Global Uncertainty

The Monetary Policy Committee (MPC) of the National Bank...

Over 180,000 Metric Tons of Fuel Failed to Arrive Due to Conflict

Minister of Trade and Regional Integration (MoTRI) , Kassahun...

Ethiopia,China Reach Final Stage of Strategic Debt Restructuring Negotiations in Beijing

A high-level Ethiopian delegation, led by Finance Minister Ahmed...

Rejoinder: Language, Identity, and the State — A Clarification

Much of the criticism directed at my argument rests...

The Satellite Saw It First: When a Distant Conflict Froze Ethiopia’s Economy

(This piece draws on preliminary findings from an ongoing...

Name:Endrias Esrael

2. Education: (የት/ት ደረጃ)     BSC in Economics 3. Company name: (የመስሪያ...
spot_img

Related Articles

Popular Categories

spot_imgspot_img