Tuesday, May 19, 2026

ደቡብ ሱዳን በ2026 የአፍሪካ ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት እንደምታስመዘግብ ተተነበየ

የአፍሪካ ደሀና በጦርነት ክፉኛ የተጎዳችው ደቡብ ሱዳን፣ እ.ኤ.አ በ2026 የነዳጅ ምርት ወደ ቀድሞ ሁኔታው በመመለሱ ምክንያት በአህጉሪቱ ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት የሚያስመዘግቡ አገራትን እንደምትመራ የዓለም ባንክ አስታወቀ።

የዓለም ባንክ ባወጣው የቅርብ ጊዜው የዓለም የኢኮኖሚ ዕድገት ትንበያ መሠረት፣ የአገሪቱ አጠቃላይ የአገር ውስጥ ምርት (GDP) በ2026 በ48.8 በመቶ ያድጋል ተብሎ ይጠበቃል።

ይህ ከፍተኛ ዕድገት የታቀደው አገሪቱ ባለፈው ዓመት ካጋጠማት የ23.8 በመቶ የኢኮኖሚ ማሽቆልቆል በኋላ መሆኑም ታውቋል።

ከፍተኛ የኢኮኖሚ ማገገም የተገኘው በሁለት ዋና ዋና ምክንያቶች እንደሆነ ሪፖርቱ ያመላክታል። የመጀመሪያው በሱዳን በኩል የሚያልፈው የነዳጅ ማስተላለፊያ ቧንቧ በመጠገኑ የነዳጅ ምርት ወደ መደበኛ ሁኔታው መመለሱ ሲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ ከአምስት ዓመታት የኢኮኖሚ ውድቀት በኋላ በአገሪቱ ውስጥ ያለው የንግድና የኢኮኖሚ እንቅስቃሴዎች መረጋጋት ነው።

ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) በበኩሉ ደቡብ ሱዳን በተጠናቀቀዉ በ2025 በ27.2 በመቶ ዕድገት እንደምታሳይ በመተንበይ የዓለም ባንክን የብሩህ ተስፋ ትንበያ አረጋግጧል። የአገሪቱ መንግሥት ገቢ ከ90 በመቶ በላይ የሚመነጨው ነዳጅ ሽያጭ እንደመሆኑ፣ የቧንቧው ጥገና ለኢኮኖሚው ትልቅ ትንፋሽ ሆኗል።

ሪፖርቱ በ2026 ሌሎች የአፍሪካ አገራት ሊያስመዘግቡት የሚችሉትን ዕድገትም ይፋ አድርጓል። በዚህም መሠረት ጊኒ በ9.3 በመቶ፣ ሩዋንዳ በ7.2 በመቶ፣ ኢትዮጵያ በ7.1 በመቶ እንዲሁም ናይጄሪያ ባለፉት አሥር ዓመታት ያላየችውን ከፍተኛ ዕድገት እንደሚያስመዘግቡ ተተንብዮአል።

በተቃራኒው እንደ ደቡብ አፍሪካ ያሉ ትልልቅ ኢኮኖሚዎች የ1.4 በመቶ ዝቅተኛ ዕድገት እንደሚያሳዩ ተጠቁሟል።

Hot this week

Production up, but the ‘cost’ variable weighs heavily

Production is up in 2021 for the Italian agricultural...

Luminos Fund’s catch-up education programs in Ethiopia recognized

The Luminos Fund has been named a top 10...

Well-planned cities essential for a resilient future in Africa concludes the World Urban Forum

The World Urban Forum (WUF) concluded today with a...

Private sector deemed key to unlocking AfCFTA potential

The private sector’s role is vital to fully unlock...

India’s Africa policy needs sustained engagement, not periodic summits

One of the persistent weaknesses of the India-Africa Forum...

Fall in Love with Impact, Not Your Organization”: The Development Sector’s Toughest Lesson

The Mastercard Foundation, a Canadian organization, celebrated its 20th...

University of Gondar, Mastercard Foundation scholars advance disability inclusion

A decade-long partnership between the University of Gondar, Queen’s...

Name: Tamiru Moges

2. Education:    Marketing Management (BA Degree) 3. Company name: B-Creative Marketing...

“Country Ownership Begins with Women’s Leadership”

In Ethiopia’s ongoing effort to strengthen its health system,...
spot_img

Related Articles

Popular Categories

spot_imgspot_img