Friday, April 3, 2026

የዩሮ ቦንድ የዕዳ ሽግሽግ ስምምነቱ ከአበዳሪዎች ኮሚቴ መመሪያ ጋር ባለመጣጣሙ እንዲቆም ተወሰነ

የገንዘብ ሚኒስቴር የሀገሪቱን የ1 ቢሊዮን ዶላር የዩሮ ቦንድ ዕዳ ለማዋቀር ከግል አበዳሪዎች ኮሚቴ ጋር ደርሶት የነበረውን የመርህ ስምምነት ተግባራዊ እንደማያደርግ በይፋ አስታወቀ።

ጥር 2 ቀን 2026 ዓ.ም የተደረሰው ይህ ስምምነት እንዲቆም የተወሰነው፣ የመንግስታት አበዳሪዎች ኮሚቴ እና ዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት ስምምነቱን መርምረው ካጠናቀቁ በኋላ ነው።

የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ አሰንደገለፁት፤ የስምምነቱ መቋረጥ ዋነኛው ምክንያት “የአበዳሪዎች የእኩልነት መርህ”  ካለመከበሩ ጋር የተያያዘ ነው። የመንግስታት አበዳሪዎች ኮሚቴስምምነቱ ከሌሎች ይፋዊ አበዳሪዎች ጋር ከተደረገው የዕዳ ሽግሽግ ማዕቀፍ ጋር እንደማይጣጣም ለኢትዮጵያ መንግስት በደብዳቤ አሳውቋል።

ይህንን ስምምነት ባለበት ሁኔታ ተግባራዊ ማድረግ ሀገሪቱ በሐምሌ ወር 2025 ዓ.ም ከአበዳሪዎች ኮሚቴ ጋር ከፈረመችው የመግባቢያ ሰነድ ጋር የሚቃረን ሆኖ ተገኝቷል።

በተጨማሪም፣ የተደረሰው ስምምነት ኢትዮጵያ ከዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት ጋር ከገባችው የኢኮኖሚ ማሻሻያ መርሃ-ግብር ግቦች እና መለኪያዎች ጋር እንደማይጣጣም ተመልክቷል።

ሚኒስቴሩ እንዳለው ከሆነ፣ ስምምነቱን መቀጠል በሀገሪቱ የማክሮ ኢኮኖሚ መረጋጋት እና በተመዘገቡ የኢኮኖሚ እድገቶች ላይ ከፍተኛ ስጋት ሊፈጥር ስለሚችል በድጋሚ መደራደር የግድ ሆኗል።

በዚህም መሠረት፣ የኢትዮጵያ መንግስት የዕዳ ሽግሽጉን የፋይናንስ ይዘት በተመለከተ ከግል አበዳሪዎች ኮሚቴ ጋር አዲስ ድርድር ለመጀመር መወሰኑን አስታውቋል።

መንግስት ውይይቱን በድጋሚ መክፈት አስፈላጊ ቢሆንም፣ በሁሉም አበዳሪዎች መካከል ፍትሃዊ የዕዳ ጫና ክፍፍልን የሚያረጋግጥ እና የሀገሪቱን የኢኮኖሚ አቅም ያገናዘበ ዘላቂ መፍትሄ ለማምጣት በቁርጠኝነት እንደሚሰራ ገልጿል።

Hot this week

Production up, but the ‘cost’ variable weighs heavily

Production is up in 2021 for the Italian agricultural...

Luminos Fund’s catch-up education programs in Ethiopia recognized

The Luminos Fund has been named a top 10...

Well-planned cities essential for a resilient future in Africa concludes the World Urban Forum

The World Urban Forum (WUF) concluded today with a...

Private sector deemed key to unlocking AfCFTA potential

The private sector’s role is vital to fully unlock...

Ethiopia, China ink deal for RMB trade settlements

To strengthen Ethiopia's financial resilience and further enhance economic...

​NEBE Warns of Election Cancellations Over Voter Registration Coercion

The National Election Board of Ethiopia (NEBE) has issued...

Bank of China, AfDB review financing framework for Bishoftu Airport

The Ethiopian Airlines Group and the Ministry of Finance...

Container Shortage Reported Due to Maritime Transport Disruptions

The Ethiopian Maritime Authority (EMA) has announced a shortage...

Ethiopia’s MPC Holds Off on Lifting Credit Cap, Citing Global Uncertainty

The Monetary Policy Committee (MPC) of the National Bank...

Over 180,000 Metric Tons of Fuel Failed to Arrive Due to Conflict

Minister of Trade and Regional Integration (MoTRI) , Kassahun...

Ethiopia,China Reach Final Stage of Strategic Debt Restructuring Negotiations in Beijing

A high-level Ethiopian delegation, led by Finance Minister Ahmed...
spot_img

Related Articles

Popular Categories

spot_imgspot_img