Wednesday, February 4, 2026

ዮሐንስ አያሌው (ዶ/ር) የፀደይ ባንክ ፕሬዝዳንት ለመሆን ከስምምነት መድረሳቸው ተገለጸ

የአማራ ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ በመሆን ሲያገለግሉ የቆዩት ዮሐንስ አያሌው (ዶ/ር)፣ በቅርቡ የፕሬዝዳንት ለውጥ ባደረገው ፀደይ ባንክ ውስጥ አቶ መኮንን የለውምወሰንን ተክተው ለመሥራት ከስምምነት ላይ መድረሳቸው ካፒታል ጋዜጣ ከምንጮቹ ተሰምቷል።

ዮሐንስ ቀደም ሲል በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ምክትል ገዥነትና ዋና ኢኮኖሚስት እንዲሁም ደግሞ በኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዝዳንትነት ያካበቱትን ሰፊ ልምድ ይዘው ከመስከረም 3 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ የአማራ ባንክን ሲመሩ የቆዩ ቢሆንም፣ አሁን ግን ወደ ፀደይ ባንክ ለመዘዋወር መወሰናቸው ታውቋል።

ይህንን ተከትሎም አማራ ባንክ ባዶ የሆነውን የዋና ሥራ አስፈጻሚ ቦታ ለመሙላት ብቁ የሆኑ አመራሮችን ለማግኘት ፍለጋ ላይ መሆኑን የውስጥ የካፒታል ምንጮች ጠቁመዋል።

የቀድሞው አማራ ብድርና ቁጠባ ተቋም ወደ ባንክነት በመሸጋገር ፀደይ ባንክ ተብሎ ከተሰየመ በኋላ፣ ባንኩን በፕሬዝዳንትነት ሲመሩ የቆዩት አቶ መኮንን የለውምወሰን በምን ምክንያት ኃላፊነታቸውን እንደለቀቁ በይፋ አልተገለጸም።

አቶ መኮንን ስራቸውን መልቀቃቸውን ተከትሎ፣ በአማራ ክልል ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ደረሰ ኃይሉ የሚመራው የባንኩ የዳይሬክተሮች ቦርድ ወ/ሮ የሺእመቤት ተፈራን በተጠባባቂ ፕሬዝዳንትነት መመደቡ ይታወሳል። ይሁን እንጂ ባንኩ አሁን ካለበት ከባድ የፋይናንስ ሁኔታ አንጻር ዶ/ር ዮሐንስን በቋሚነት ለመሾም ስምምነት ላይ መደረሱ ተመልክቷል።

ፀደይ ባንክ በቅርቡ ይፋ ባደረገው የ2017 የሒሳብ ዓመት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት መሠረት፣ 2.13 ቢሊዮን ብር የሚጠጋ ከፍተኛ ኪሳራ ማጋጠሙን አስታውቋል።

ይህ ከፍተኛ የፋይናንስ ክፍተት ባጋጠመበት ወቅት ዶ/ር ዮሐንስ ወደ አመራርነት መምጣታቸው፣ ባንኩን ከኪሳራ ለማውጣትና ወደ ትርፋማነት ለመመለስ ካለው ከፍተኛ ተስፋ የመነጨ እንደሆነ ይገመታል።

Hot this week

Production up, but the ‘cost’ variable weighs heavily

Production is up in 2021 for the Italian agricultural...

Luminos Fund’s catch-up education programs in Ethiopia recognized

The Luminos Fund has been named a top 10...

Well-planned cities essential for a resilient future in Africa concludes the World Urban Forum

The World Urban Forum (WUF) concluded today with a...

Private sector deemed key to unlocking AfCFTA potential

The private sector’s role is vital to fully unlock...

በአንድ ሳምንት ልዩነት የዶላር ዋጋ ጭማሪ አሳየ፤ ከፍተኛው መግዣ 155.05 ብር ደረሰ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በሕገ-ወጥ የውጭ ምንዛሬ ገበያ ላይ የታየውን...

መንግሥት በነዳጅ ላይ ሲያደርግ የነበረውን ድጎማ እስከ መጪው የካቲት ወር ሙሉ በሙሉ ሊያነሳ ነው

መንግሥት ላለፉት አራት ዓመታት በነዳጅ ምርቶች ላይ ሲያደርግ የነበረውን...

Six African cities take stock of fiscal reforms in drive toward sustainable urban finance

City leaders and finance officials from across the continent...

KOICA strengthens WFP’s efforts to prevent malnutrition in Ethiopia

The United Nations World Food Programme (WFP) has welcomed a...

ECA, Morocco sign host agreement ahead of 2026 conference of ministers

UN Economic Commission for Africa Executive Secretary, Claver Gatete...
spot_img

Related Articles

Popular Categories

spot_imgspot_img