Wednesday, September 16, 2026

በኢትዮጵያ የሚገኘውን የኩርሙክ ወርቅ ማዕድን የሚያለማው አላይድ ጎልድ በ5.5 ቢሊዮን የካናዳ ዶላር ሊሸጥ ነው

በኢትዮጵያ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኘውን ግዙፉን የኩርሙክ የወርቅ ማዕድን ፕሮጀክት ጨምሮ በአፍሪካ ሦስት ዋና ዋና ይዞታዎች ያሉት አላይድ ጎልድ ኮርፖሬሽን በቻይናው የማዕድን ግዙፍ ዚጂን ጎልድ ለመገዛት ስምምነት ላይ መድረሱን አስታወቀ።

ካፒታል ጋዜጣ ዛሬ ጥር 18 ቀን 2018 ዓ.ም. ከወጣው መረጃ ላይ እንደተመለከተው፣ ዚጂን ጎልድ አላይድ ጎልድን በ5.5 ቢሊዮን የካናዳ ዶላር (በግምት 4 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር) በጥሬ ገንዘብ ለመግዛት የመጨረሻ ስምምነት ተፈራርሟል። ይህ ግብይት በአፍሪካ የማዕድን ዘርፍ በዓመቱ ከተመዘገቡት ትልልቅ ግዥዎች አንዱ ሆኖ ተመዝግቧል።

በሆንግ ኮንግ የአክሲዮን ገበያ የተመዘገበውና የገበያ ዋጋው በግምት 70 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር የሆነው ግዙፉ ዚጂን ጎልድ፣ በዚህ ግዥ አማካኝነት በአፍሪካ ያለውን ተደራሽነት በከፍተኛ ሁኔታ ያጠናክራል ተብሏል።

በስምምነቱ መሠረት ዚጂን ጎልድ ለእያንዳንዱ የአላይድ ጎልድ አክሲዮን 44 የካናዳ ዶላር በጥሬ ገንዘብ የሚከፍል ሲሆን፣ ይህም ኩባንያው ባለፉት 30 ቀናት በገበያ ላይ ከነበረው አማካይ ዋጋ የ27 በመቶ ብልጫ አለው። ይህ ከፍተኛ ዋጋ የቀረበው አላይድ ጎልድ ላለፉት ሁለት ዓመታት ሲያካሂድ የነበረው ስትራቴጂካዊ የንግድ ክለሳ ውጤት መሆኑ ተገልጿል።

የዚጂን ጎልድ ሊቀመንበር ሆንግፉ ሊን እንደገለጹት፣ ይህ ግዥ ኩባንያቸው በአፍሪካ ያለውን ተጽዕኖ በከፍተኛ ሁኔታ ያሳድገዋል። በተለይም በኢትዮጵያ የሚገኘውን የኩርሙክ ወርቅ ፕሮጀክት እና በማሊ የሚገኘውን የሳዲዮላ ፕሮጀክት ለብዙ አሥርተ ዓመታት ምርት የሚሰጡ “የትውልድ ሀብቶች” ሲሉ ጠርተዋቸዋል።

ሊቀመንበሩ አክለውም “እንደ አዲስ ባለቤት፣ በኢትዮጵያ፣ በማሊ እና በኮትዲቩዋር ከሚገኙ ባለድርሻ አካላት ጋር እነዚህን ፕሮጀክቶች የበለጠ ለማሳደግ በጉጉት እንጠብቃለን” ብለዋል።

የአላይድ ጎልድ ሊቀመንበርና ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፒተር ማሮን በበኩላቸው፣ “ይህ ግብይት ለአክሲዮን ባለቤቶቻችን ከፍተኛና ፈጣን የጥሬ ገንዘብ ጥቅም የሚያስገኝ ነው” ብለዋል። ግዥው ኩባንያው በአፍሪካ የገነባው ዓለም አቀፍ ደረጃ ያለው የማዕድን ይዞታ ውጤታማ መሆኑን የሚያረጋግጥ እንደሆነም ገልጸዋል።

ግዥው ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ የሚመነዘረው እስከ ሚያዝያ 2026 መጨረሻ ድረስ ይሆናል። ይሁን እንጂ ስምምነቱ እንዲጠናቀቅ የአላይድ ጎልድ ባለአክሲዮኖች በልዩ ስብሰባ በ66.6 በመቶ ድምፅ ግዥውን ማጽደቅ ይኖርባቸዋል።

ከዚህ በተጨማሪም የካናዳ ፍርድ ቤት እና የኢንቨስትመንት ቁጥጥር ተቋማት ፈቃድ ማግኘት እና የኢትዮጵያ፣ የማሊ እና የኮትዲቩዋር መንግስታት እንዲሁም የቻይና የቁጥጥር ተቋማት ይሁንታ እንደሚያስፈልግ ተገልጿል።

ግብይቱ እንደተጠናቀቀ አላይድ ጎልድ በቶሮንቶ እና በኒውዮርክ የአክሲዮን ገበያዎች የነበረው ምዝገባ የሚሰረዝ ሲሆን፣ ኩባንያው ሙሉ በሙሉ በዚጂን ጎልድ ስር ሆኖ ሥራውን ይቀጥላል።

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ግንባታው በመጠናቀቅ ላይ ያለው ኩርሙክ ወርቅ፣ ኢትዮጵያ በወርቅ ልማት የዓለም ካርታን እንደምትቀላቀል ማሳያ ሆኗል። ኩርሙክ ወርቅ ለ12 ዓመታት ወርቅ ማልማት የሚያስችል ክምችት ያለው ሲሆን፣ በዓመት እስከ 9 ቶን በላይ ወርቅ እንደሚያመርት ይጠበቃል።

ከ500 ሚሊዮን ዶላር በላይ ኢንቨስት እየተደረገበት ያለው ይህ ፕሮጀክት በቅርቡ ወደ ማምረት እንደሚገባ ይጠበቃል።

Hot this week

Production up, but the ‘cost’ variable weighs heavily

Production is up in 2021 for the Italian agricultural...

Luminos Fund’s catch-up education programs in Ethiopia recognized

The Luminos Fund has been named a top 10...

Well-planned cities essential for a resilient future in Africa concludes the World Urban Forum

The World Urban Forum (WUF) concluded today with a...

Private sector deemed key to unlocking AfCFTA potential

The private sector’s role is vital to fully unlock...

Ethiopia, Kenya finalize preparations to scale up cross-border power trade by December 2026

Ethiopia is finalizing preparations to double its electricity supply...

Ethiopia records 824% remittance growth over the decade, accounting for 5% of national GDP

Ethiopia has rapidly ascended to become Africa’s fourth-largest remittance...

Ethiopia Rejects Commercial Buyback Offer for Looted 18th-Century Royal Gospel

The Ethiopian Heritage Authority has confirmed to Capital that...

Djibouti positions itself as Horn of Africa logistics gateway with new WFP base handover

The Government of Djibouti has officially assumed full management...

Dangote Refinery launches historic $1.6B IPO

The Nigerian Exchange (NGX) officially launched the initial public...

IOM warns Sudan humanitarian system faces collapse within weeks without new funding

The International Organization for Migration (IOM) has issued an...

Safaricom surpasses 15 million subscribers as it marks five years

Safaricom is marking five years since it received a...

Africa’s economic momentum is building as savings and cross-border trade activity accelerate

Rising savings, increasing cross-border payment activity and growing participation...
spot_img

Related Articles

Popular Categories

spot_imgspot_img