Saturday, December 13, 2025

በኢትዮጵያ የሚገኙ ሱዳናውያን በጦርነትና በገቢ እጦት መካከል 300 ዶላር ቅጣት እየተጠየቁ ነው

ተባለበኢትዮጵያ የሚገኙ በጦርነት የተፈናቀሉ ሱዳናውያን፣ ከሰብዓዊ እና ከኑሮ ፈተናዎች በተጨማሪ፣ የመኖሪያ ፈቃድ እና የቪዛ እድሳት ጋር ተያይዘው ከባድ የገንዘብ ጫና እየደረሰባቸው መሆኑን ተገልጿል።

የቅርብ ጊዜ መረጃዎች እንደሚያሳዩት ግጭቱ ከጀመረ ወዲህ ኢትዮጵያ ከ100 ሺህ በላይ ሱዳናውያንን ተቀብላለች። ዜጎቹ እንደሚሉት፣ ባለሥልጣናት ለእያንዳንዱ ወርሃዊ ቪዛ እድሳት 100 ዶላር ክፍያ የሚጠይቁ ሲሆን፣ እድሳቱን በማዘግየት ለእያንዳንዱ ወር ደግሞ 300 ዶላር ቅጣት ይጥላሉ።

የሱዳን ትሪቢዩን ዘገባ እንደሚያሳየው፣ ወርሃዊ የመግቢያ ቪዛዎችን ማደስ በጦርነት፣ በገቢ መጥፋት እና በሀብት እጥረት መካከል እጅግ በጣም አድካሚና ውድ ሂደት ሆኗል።

በተለይም ጦርነቱ በቀጠለበት በዚህ ወቅት፣ ይህ የገንዘብ ክፍያና ቅጣት ከሱዳናውያን ስቃይ ጋር የሚጣጣም ባለመሆኑ፣ የሰብዓዊ ውሳኔ እንዲሰጥና ጣልቃ ገብነት እንዲደረግ ጥሪ ቀርቧል።

ሱዳናውያኑ አክለውም፣ ቪዛ የማራዘም ሂደት ላይ ካለው ከፍተኛ ክፍያና ቅጣት በተጨማሪ፣ በአዲስ አበባ የሚገኘው የሱዳን ኤምባሲ ለችግሮቻቸው ተገቢ ምላሽ እየሰጠ አለመሆኑን ተችተዋል። ዘገባዉ ፤ ዜጎቹ ኤምባሲው ለከፍተኛ ችግሮች፣ ለምሳሌም ለምግብ እና ለመድሃኒት እጥረት፣ ምላሽ እንደማይሰጥ እና ሰራተኞቹም በአካል ተገኝተው የዜጎችን ሁኔታ ክትትል እንደማያደርጉ አስረድቷል።

ሱዳናውያኑ፣ ቀደም ሲል እንደተደረገው፣ የኢትዮጵያ መንግስት ጣልቃ በመግባት ለሱዳናውያን የስደተኞችን ሁኔታ ከግምት ውስጥ ያስገባ የዘጠኝ ወር የቪዛ ነፃ ፈቃድ እንዲሰጥላቸው ጠይቀዋል።

Hot this week

Production up, but the ‘cost’ variable weighs heavily

Production is up in 2021 for the Italian agricultural...

Luminos Fund’s catch-up education programs in Ethiopia recognized

The Luminos Fund has been named a top 10...

Well-planned cities essential for a resilient future in Africa concludes the World Urban Forum

The World Urban Forum (WUF) concluded today with a...

Private sector deemed key to unlocking AfCFTA potential

The private sector’s role is vital to fully unlock...

የወጪ ንግድ ኮንትራት ምዝገባና የመላኪያ ፈቃድ አገልግሎት ከመጪው ሰኞ ጀምሮ በኦላይን ሊሆን ነዉ

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ለንግዱ ማኅበረሰብ የሚሰጠውን የሁለት ወሳኝ...

IMF Urges Ethiopia to Deepen Forex Reforms, Maintain Fiscal Discipline

The International Monetary Fund (IMF) has called on Ethiopia...

How Smarter Business Operations Lead to Long-Term Growth

You will find that most business owners spend the...

አይኤምኤፍ ለኢትዮጵያ 261 ሚሊዮን ዶላር እንዲለቀቅ የባለሞያዎች ደረጃ ስምምነት ላይ ደረሰ

ዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (አይኤምኤፍ) ከኢትዮጵያ ጋር በ3.4 ቢሊዮን...

ሁሉም ባንኮች አዲስ እና ነባር ሂሳቦችን ለማስተሳሰር ወደ VeriFayda 2 እንዲሸጋገሩ ተወሰነ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እና የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም፣ የፋይዳ ዲጂታል...

NBE orders financial institutions to link accounts with Fayda ID

The National Bank of Ethiopia (NBE) has ordered all...

TECNO’s AFCON-Ready AI Features Reflect a New Era in Mobile Sports Viewing

#Advertorial TECNO, official CAF global partner, introduces four intelligent tools...

Instant Payments, Big Data & High Availability: Why Banks in Ethiopia Need a Robust Data Backbone

By Demos Kyriacou Instant payments, big data and high availability...
spot_img

Related Articles

Popular Categories

spot_imgspot_img