Saturday, December 13, 2025

ገቢዎች ሚኒስቴር ከ50 ሺህ ብር በላይ ግብይት ላይ የተሰጠውን የቫት ማቀናነስ ማብራሪያ ‘ለጊዜው ተፈጻሚ አይደረግ’ አለ

ገቢዎች ሚኒስቴር ከ50 ሺህ ብር በላይ በሆነ ጥሬ ገንዘብ የሚፈጸሙ የንግድ ግብይቶችን በተመለከተ የገንዘብ ሚኒስቴር ከሰሞኑ የሰጠውን ማብራሪያ በከፊል አግደ። በተለይም የተጨማሪ እሴት ታክስ (ቫት) ማቀናነስ/ተመላሽ ጉዳይ ላይ የተሰጠው ማብራሪያ “ለጊዜው ተፈጻሚ እንዳይደረግ” የሚል መመሪያ አስተላልፏል።

የገንዘብ ሚኒስቴር በጥቅምት 27 ቀን 2018 ዓ.ም. ማብራሪያው፣ በገቢ ግብር ማሻሻያ አዋጅ ቁጥር 1395/2017 የተቀመጠው ከ50 ሺህ ብር በላይ የጥሬ ገንዘብ ግብይት ገደብ ተፈፃሚ የሚሆነው ለገቢ ግብር ብቻ መሆኑንና የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) የግብዓት ታክስ የማቀናነስ መብትን እንደማይገድብ በዝርዝር አስቀምጦ ነበር።

በተጨማሪም፣ ገዥዎች ከገደቡ በላይ በጥሬ ገንዘብ ከከፈሉ፣ ትርፍ ግብር በሚሰላበት ጊዜ ትርፍ ክፍያው እንደተቀናሽ ወጪ እንደማይያዝ እንዲሁም ሻጮችም ከገደቡ በላይ ጥሬ ገንዘብ ከተቀበሉ እኩል የገንዘብ ቅጣት እንደሚጠብቃቸው አስታውቆ እንደነበር ይታወሳል።ሆኖም የገቢዎች ሚኒስቴር በጥቅምት 29 ቀን 2018 ዓ.ም. ባስተላለፈው የሰርኩላር ደብዳቤ ፤ የገንዘብ ሚኒስቴር የሰጠው የቫት ማቀናነስ ማብራሪያ አዋጁ የተፈለገበትን “የታክስ ስወራ ድርጊት ለማስቀረት” የሚለውን ዓላማ “በአግባቡ ያልተመለከተ” በመሆኑ ውይይት እንዲደረግበት በመግለፅ  ” የቫት ማቀናነስ/ተመላሽ ጉዳይ ለጊዜው ተፈጻሚ እንዳይደረግ አዟል።

በገቢ ግብር አዋጁ ላይ የተቀመጡት ሌሎች የጥሬ ገንዘብ ገደቦች፣ በተለይም ገዥዎች የተቀናሽ ወጪ መብታቸውን የሚያጡበት እና ሻጮች ቅጣት የሚጣልባቸው ድንጋጌዎች፣ ተግባራዊ እንደሚሆኑ ሚኒስትሩ አስታውቋል።በተጨማሪም፣ የገቢዎች ሚኒስቴር ገቢ ወይም ሽያጭ የለንም በማለት ባዶ የሚያሳውቁ ታክስ ከፋዮችን አነስተኛ አማራጭ ግብር ለማስከፈል የሚያስችል ዝርዝር ማብራሪያ ከገንዘብ ሚኒስቴር እስኪመጣ ድረስ፣ ቀደም ሲል በተሰጠው አሰራር እንዲስተናገዱ ማዘዙን ለካፒታል የደረሰው የአፈፃፀም መመሪያው ያመለክታል።

Hot this week

Production up, but the ‘cost’ variable weighs heavily

Production is up in 2021 for the Italian agricultural...

Luminos Fund’s catch-up education programs in Ethiopia recognized

The Luminos Fund has been named a top 10...

Well-planned cities essential for a resilient future in Africa concludes the World Urban Forum

The World Urban Forum (WUF) concluded today with a...

Private sector deemed key to unlocking AfCFTA potential

The private sector’s role is vital to fully unlock...

የወጪ ንግድ ኮንትራት ምዝገባና የመላኪያ ፈቃድ አገልግሎት ከመጪው ሰኞ ጀምሮ በኦላይን ሊሆን ነዉ

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ለንግዱ ማኅበረሰብ የሚሰጠውን የሁለት ወሳኝ...

IMF Urges Ethiopia to Deepen Forex Reforms, Maintain Fiscal Discipline

The International Monetary Fund (IMF) has called on Ethiopia...

How Smarter Business Operations Lead to Long-Term Growth

You will find that most business owners spend the...

አይኤምኤፍ ለኢትዮጵያ 261 ሚሊዮን ዶላር እንዲለቀቅ የባለሞያዎች ደረጃ ስምምነት ላይ ደረሰ

ዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (አይኤምኤፍ) ከኢትዮጵያ ጋር በ3.4 ቢሊዮን...

ሁሉም ባንኮች አዲስ እና ነባር ሂሳቦችን ለማስተሳሰር ወደ VeriFayda 2 እንዲሸጋገሩ ተወሰነ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እና የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም፣ የፋይዳ ዲጂታል...

NBE orders financial institutions to link accounts with Fayda ID

The National Bank of Ethiopia (NBE) has ordered all...

TECNO’s AFCON-Ready AI Features Reflect a New Era in Mobile Sports Viewing

#Advertorial TECNO, official CAF global partner, introduces four intelligent tools...

Instant Payments, Big Data & High Availability: Why Banks in Ethiopia Need a Robust Data Backbone

By Demos Kyriacou Instant payments, big data and high availability...
spot_img

Related Articles

Popular Categories

spot_imgspot_img