Monday, December 29, 2025

በትግራይ የካናዳ ኩባንያ ማዕድን ቦታዎች ላይ ህገወጥ የማዕድን ቁፋሮ ተጧጡፏል ሲል አዲስ ጥናት አመለከተ

በኢያሱ ዘካርያስ

በትግራይ ክልል ውስጥ ከሁለት ዓመታት የእርስ በርስ ግጭት በኋላ፣ በዓለም አቀፍ ላይ የሚስተዋለዉን የወርቅ ዋጋ መናር ተከትሎ በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር የሚያንቀሳቅስ ሕገ-ወጥ የወርቅ ንግድ መፋፋሙን አዲስ የጋራ ምርመራ አመለከተ።

ምርመራው እንደሚያመለክተው፣ የካናዳው ኩባንያ ኢስት አፍሪካ ሜታልስ ንብረት በሆኑት ማቶ ቡላ እና ዳ ታምቡክ ማዕድን ቦታዎች ላይ ሕገወጥ የማዕድን ማውጣት ተግባር በስፋት እየተፈጸመ ነው።

ዘ ግሎብ ኤንድ ሜይል ከ ቡሮ ኦፍ ኢንቨስቲጌቲቭ ጆርናሊዝም ጋር ባደረጉት ምርመራ መሠረት፣ ሥራ ያልጀመሩና ተደራሽ አይደሉም የተባሉት እነዚህ ቦታዎች ላይ፣ የቀድሞ ወታደሮች እና የቻይና ማዕድን ቆፋሪዎች ስማቸው ያልተገለጸ ባለሀብቶች ድጋፍ አግኝተው ከ2024 መጀመሪያ አንስቶ እስከ 2025 አጋማሽ ድረስ ወርቅ ሲያወጡ ቆይተዋል።

ሪፖርቱ በክልሉ ከጦርነቱ በኋላ በተፈጠረው የፖለቲካ ክፍተት ሳቢያ ያልተገደበ የማዕድን ማውጣት ኢኮኖሚ መጧጧፉን ያሳያል። ወታደራዊ ቡድኖች እና የአካባቢ አዛዦች ቁልፍ የማዕድን ክምችቶችንና የኮንትሮባንድ መንገዶችን በመቆጣጠር፣ ሕገወጥ ቁፋሮው እንዲስፋፋና የክልሉ ሀብት በቁጥጥር ስር በሌለ መንገድ እንዲባክን ምክንያት ሆነዋል።

የወርቅ ዋጋ በዓለም ገበያ በዚህ ዓመት ብቻ ከ50% በላይ መጨመሩ ዋናው ማነቃቂያ ሲሆን፣ ክልሉ የአካባቢው ማህበረሰብ ተጠቃሚነት ሳይረጋገጥ ወደ “ሱዳን መሰል የሀብት ግጭት” ሊያመራ የሚችል አደጋ ተጋርጦበታል ተብሏል።

የቀድሞ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ ፕሬዝዳንት የነበሩት አቶ ጌታቸው ረዳ ሕገወጥ ተግባሩን ለማስቆም እና ንብረቶችን ለመያዝ ግብረ ኃይል ቢሰማሩም፣ በደቡባዊው የክልሉ ክፍል እየተባባሰ ያለው ግጭት የማስፈጸም ስራውን አደጋ ላይ እየጣለው መሆኑ ተገልጿል።

በ2017 በጀት ዓመት 10 ወራት ብቻ ከትግራይ ክልል ለብሔራዊ ባንክ ከ12 ሺህ 210 ኪሎ ግራም በላይ ወርቅ ገቢ የተደረገ ሲሆን፣ ይህም ከሌሎች ክልሎች የሚበልጥ ሆኖ መመዝገቡ ይታወሳል።

የቫንኩቨሩ ኩባንያ ኢስት አፍሪካ ሜታልስ፣ ሁለቱን ፕሮጀክቶች ለማልማት ከቻይናው ቲቤት ሁዋዩ ማይኒንግ ጋር እንደሚሰራ አስታውቋል። የቻይናው አጋር ፕሮጀክቶቹ ሙሉ ፍቃድ ያላቸው መሆናቸውንና ለምርት ዝግጁ እስኪሆኑ ድረስ 100% የልማት ወጪዎችን እንደሚሸፍን ኩባንያው ገልጿል።

ይሁን እንጂ፣ ኢስት አፍሪካ ሜታልስ በየትኛውም ሕገወጥ ተግባር ውስጥ እንዳልተሳተፈ በመግለጽ፣ የቻይና አጋሮቹም ሕገወጥ ቁፋሮዎችን ፈጽመዋል የሚለውን ክስ ውድቅ አድርጓል። ሆኖም ባለሙያዎች እንደሚሉት፣ ከሲልክ ሮድ ኢንቨስትመንትስ እና ከትግራይ ሪሶርስስ ጋር ግንኙነት ያላቸው የቻይና ቡድኖች በእነዚህ ቦታዎች ላይ ወርቅ ሲያወጡ መቆየታቸውን አመልክተዋል።

Hot this week

Production up, but the ‘cost’ variable weighs heavily

Production is up in 2021 for the Italian agricultural...

Luminos Fund’s catch-up education programs in Ethiopia recognized

The Luminos Fund has been named a top 10...

Well-planned cities essential for a resilient future in Africa concludes the World Urban Forum

The World Urban Forum (WUF) concluded today with a...

Private sector deemed key to unlocking AfCFTA potential

The private sector’s role is vital to fully unlock...

The unnoticed acts of adjustment in Public Transport

Progress in life rarely stems from rigid ideals; it...

Name:Belen Alem

2. የትምህርት ደረጃ (Education):      Advanced Degree 3. የድርጅቱ ስም (Company...

From ambition to delivery

What Ethiopia can learn from Africa's Climate Finance Pioneers Ethiopia...

How social media is destroying the youth

Social media's relentless grip is ravaging a generation of...

All-in-One Practice Management

As African law firms race to digitize their operations,...
spot_img

Related Articles

Popular Categories

spot_imgspot_img