Saturday, May 2, 2026

ኢትዮጵያ አየር መንገድ እና ፍላይዱባይ የሶማሊያ ኢ-ቪዛ ለሶማሊላንድ በረራዎች እንደማይሠራ አረጋገጡ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ እና ፍላይዱባይ (FlyDubai) ወደ ሶማሊላንድ ለሚደረጉ በረራዎች የጉዞ መመሪያዎቻቸውን በማዘመን፣ የሶማሊያ የኤሌክትሮኒክስ ቪዛ (ኢ-ቪዛ) መስፈርት በሃርጌሳ እና በበርበራ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያዎች ላይ እንደማይሠራ በይፋ አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ እንዳስታወቀው “የሶማሊያ የኢ-ቪዛ መስፈርቶች ወደ በርበራ ወይም ሃርጌሳ ለሚመጡ ተሳፋሪዎች አይሰራም” በማለት ገልጿል። አየር መንገዱ ወደ ሶማሊላንድ የሚጓዙ ተሳፋሪዎች ሲደርሱ ቪዛ ማግኘት እንደሚችሉ አፅንኦት ሰጥቷል።

ፍላይዱባይ በተመሳሳይ የጉዞ ማስጠንቀቂያውን በማሻሻል፣ መንገደኞች በሃርጌሳ እና በበርበራ ሲደርሱ ቪዛ ማግኘት እንደሚችሉ አረጋግጧል። ይህ እርምጃ ዓለም አቀፉ የአየር ትራንስፖርት ማህበር (IATA)ን ጨምሮ በርካታ አካላት የሶማሊላንድን የኢሚግሬሽን ቁጥጥር ከሶማሊያ ሥርዓት በመለየት የጉዞ መመሪያዎችን ካወጡ በኋላ የተወሰደ ነው።

ከዚህ በተጨማሪም የአየር መንገዶቹ መመሪያዎች መሻሻል የተከሰተው ዩናይትድ ስቴትስ በሶማሊያ የኢ-ቪዛ ሲስተም ላይ ትልቅ የደኅንነት ጥሰት ከተፈጸመ በኋላ ባወጣችዉ አስቸኳይ ማስጠንቀቂያ ነዉ።

በሶማሊያ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ እንዳረጋገጠው፣ ጠላፊዎች የሶማሊያን የኢ-ቪዛ መድረክ ሰብረው በመግባት ቢያንስ የ35,000 አመልካቾችን የግል መረጃ ተጋልጧል።

ከዚህ ከተጋለጡት መረጃዎች መካከል በሺዎች የሚቆጠሩ የአሜሪካ ዜጎችን ጨምሮ ስም፣ የፓስፖርት ፎቶዎች፣ የትውልድ ቀኖች፣ የኢሜይል አድራሻዎች እና የመኖሪያ አድራሻዎች ይገኙበታል ተብሏል።

የአሜሪካ መንግሥት የሶማሊያን ኢ-ቪዛ ሲስተም የተጠቀሙ ዜጎቹን በአስቸኳይ በአቅራቢያቸው የሚገኘውን ኤምባሲያቸውን እንዲያነጋግሩ እና ማንኛውንም አጠራጣሪ እንቅስቃሴ እንዲከታተሉ አሳስቧል።

ባለሞያዎች እንደሚሉት፣ በሶማሊያ ሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣን እና በሱማሊላንድ መንግስት መካከል በአቪዬሽን ቁጥጥር ዙሪያ የሚታየው ውጥረት በሁለቱ አካላት ስልጣን ላይ የሚደረግ የፖለቲካ ትግል ማሳያ ነው።

ለዚህ ዉጥረት መነሻዉ የሶማሊያ አቋም መላውን የአየር ክልል የመቆጣጠር ስልጣን የእኔ ነው የሚል ሲሆን፣ ይህንንም ለማስፈጸም ወደ ሀርጌሳ ለሚጓዙ ሁሉም ተሳፋሪዎች የሶማሊያ ኢ-ቪዛ እንዲኖራቸው አዟል። በሌላ በኩል፣ የሶማሊላንድ አቋም ደግሞ ራሷን የቻለች ሀገር በመሆኗ የአየር ክልሏን በሙሉ የመቆጣጠር መብት እንዳላት ትናገራለች።

በዚህ መሠረት፣ ዓለም አቀፍ አየር መንገዶች በሰማሊላንድ አየር ማረፊያዎች (እንደ ሀርጌሳ) ከማረፋቸው በፊት ከራሱ የክልል ባለሥልጣናት የቅድሚያ ፈቃድ እንዲያገኙ በማዘዝ፣ የሶማሊያን ኢ-ቪዛ ሕገ-ወጥ መሆኑን በመቃወም በአንድ ክልል ላይ የቁጥጥር ስልጣንን ለመጠየቅ የሚያደርጉትን ጥረት በተግባር እያሳዩ መሆኑ ተመላክቷል።

Hot this week

Production up, but the ‘cost’ variable weighs heavily

Production is up in 2021 for the Italian agricultural...

Luminos Fund’s catch-up education programs in Ethiopia recognized

The Luminos Fund has been named a top 10...

Well-planned cities essential for a resilient future in Africa concludes the World Urban Forum

The World Urban Forum (WUF) concluded today with a...

Private sector deemed key to unlocking AfCFTA potential

The private sector’s role is vital to fully unlock...

Binance Announces Suspension of Crypto Trading Services Birr

The world’s largest cryptocurrency exchange, Binance, has officially announced...

New draft proclamation opens insurance sector to foreign investment

Ethiopia officially plans to open its insurance sector to...

Penthouse Apartment for Rent – Prime Bole Location

Experience elevated living in this stunning penthouse apartment located...

REQUEST FOR EXPRESSION OF INTEREST (EOI)

This notice is placed by UNECA. The accuracy, reliability...

INVITATION TO BID

SALE OF OBSOLETE FURNITURE AND SCRAP. R EF# P RO3...

Invitation For Bid

The International Rescue Committee (IRC) is one of the...

Invitation to Bid : Bid No. HB/­030/2026

Hibret Bank would like to invite interested Local and...
spot_img

Related Articles

Popular Categories

spot_imgspot_img