Saturday, December 13, 2025

በትግራይ የካናዳ ኩባንያ ማዕድን ቦታዎች ላይ ህገወጥ የማዕድን ቁፋሮ ተጧጡፏል ሲል አዲስ ጥናት አመለከተ

በኢያሱ ዘካርያስ

በትግራይ ክልል ውስጥ ከሁለት ዓመታት የእርስ በርስ ግጭት በኋላ፣ በዓለም አቀፍ ላይ የሚስተዋለዉን የወርቅ ዋጋ መናር ተከትሎ በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር የሚያንቀሳቅስ ሕገ-ወጥ የወርቅ ንግድ መፋፋሙን አዲስ የጋራ ምርመራ አመለከተ።

ምርመራው እንደሚያመለክተው፣ የካናዳው ኩባንያ ኢስት አፍሪካ ሜታልስ ንብረት በሆኑት ማቶ ቡላ እና ዳ ታምቡክ ማዕድን ቦታዎች ላይ ሕገወጥ የማዕድን ማውጣት ተግባር በስፋት እየተፈጸመ ነው።

ዘ ግሎብ ኤንድ ሜይል ከ ቡሮ ኦፍ ኢንቨስቲጌቲቭ ጆርናሊዝም ጋር ባደረጉት ምርመራ መሠረት፣ ሥራ ያልጀመሩና ተደራሽ አይደሉም የተባሉት እነዚህ ቦታዎች ላይ፣ የቀድሞ ወታደሮች እና የቻይና ማዕድን ቆፋሪዎች ስማቸው ያልተገለጸ ባለሀብቶች ድጋፍ አግኝተው ከ2024 መጀመሪያ አንስቶ እስከ 2025 አጋማሽ ድረስ ወርቅ ሲያወጡ ቆይተዋል።

ሪፖርቱ በክልሉ ከጦርነቱ በኋላ በተፈጠረው የፖለቲካ ክፍተት ሳቢያ ያልተገደበ የማዕድን ማውጣት ኢኮኖሚ መጧጧፉን ያሳያል። ወታደራዊ ቡድኖች እና የአካባቢ አዛዦች ቁልፍ የማዕድን ክምችቶችንና የኮንትሮባንድ መንገዶችን በመቆጣጠር፣ ሕገወጥ ቁፋሮው እንዲስፋፋና የክልሉ ሀብት በቁጥጥር ስር በሌለ መንገድ እንዲባክን ምክንያት ሆነዋል።

የወርቅ ዋጋ በዓለም ገበያ በዚህ ዓመት ብቻ ከ50% በላይ መጨመሩ ዋናው ማነቃቂያ ሲሆን፣ ክልሉ የአካባቢው ማህበረሰብ ተጠቃሚነት ሳይረጋገጥ ወደ “ሱዳን መሰል የሀብት ግጭት” ሊያመራ የሚችል አደጋ ተጋርጦበታል ተብሏል።

የቀድሞ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ ፕሬዝዳንት የነበሩት አቶ ጌታቸው ረዳ ሕገወጥ ተግባሩን ለማስቆም እና ንብረቶችን ለመያዝ ግብረ ኃይል ቢሰማሩም፣ በደቡባዊው የክልሉ ክፍል እየተባባሰ ያለው ግጭት የማስፈጸም ስራውን አደጋ ላይ እየጣለው መሆኑ ተገልጿል።

በ2017 በጀት ዓመት 10 ወራት ብቻ ከትግራይ ክልል ለብሔራዊ ባንክ ከ12 ሺህ 210 ኪሎ ግራም በላይ ወርቅ ገቢ የተደረገ ሲሆን፣ ይህም ከሌሎች ክልሎች የሚበልጥ ሆኖ መመዝገቡ ይታወሳል።

የቫንኩቨሩ ኩባንያ ኢስት አፍሪካ ሜታልስ፣ ሁለቱን ፕሮጀክቶች ለማልማት ከቻይናው ቲቤት ሁዋዩ ማይኒንግ ጋር እንደሚሰራ አስታውቋል። የቻይናው አጋር ፕሮጀክቶቹ ሙሉ ፍቃድ ያላቸው መሆናቸውንና ለምርት ዝግጁ እስኪሆኑ ድረስ 100% የልማት ወጪዎችን እንደሚሸፍን ኩባንያው ገልጿል።

ይሁን እንጂ፣ ኢስት አፍሪካ ሜታልስ በየትኛውም ሕገወጥ ተግባር ውስጥ እንዳልተሳተፈ በመግለጽ፣ የቻይና አጋሮቹም ሕገወጥ ቁፋሮዎችን ፈጽመዋል የሚለውን ክስ ውድቅ አድርጓል። ሆኖም ባለሙያዎች እንደሚሉት፣ ከሲልክ ሮድ ኢንቨስትመንትስ እና ከትግራይ ሪሶርስስ ጋር ግንኙነት ያላቸው የቻይና ቡድኖች በእነዚህ ቦታዎች ላይ ወርቅ ሲያወጡ መቆየታቸውን አመልክተዋል።

Hot this week

Production up, but the ‘cost’ variable weighs heavily

Production is up in 2021 for the Italian agricultural...

Luminos Fund’s catch-up education programs in Ethiopia recognized

The Luminos Fund has been named a top 10...

Well-planned cities essential for a resilient future in Africa concludes the World Urban Forum

The World Urban Forum (WUF) concluded today with a...

Private sector deemed key to unlocking AfCFTA potential

The private sector’s role is vital to fully unlock...

የወጪ ንግድ ኮንትራት ምዝገባና የመላኪያ ፈቃድ አገልግሎት ከመጪው ሰኞ ጀምሮ በኦላይን ሊሆን ነዉ

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ለንግዱ ማኅበረሰብ የሚሰጠውን የሁለት ወሳኝ...

IMF Urges Ethiopia to Deepen Forex Reforms, Maintain Fiscal Discipline

The International Monetary Fund (IMF) has called on Ethiopia...

How Smarter Business Operations Lead to Long-Term Growth

You will find that most business owners spend the...

አይኤምኤፍ ለኢትዮጵያ 261 ሚሊዮን ዶላር እንዲለቀቅ የባለሞያዎች ደረጃ ስምምነት ላይ ደረሰ

ዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (አይኤምኤፍ) ከኢትዮጵያ ጋር በ3.4 ቢሊዮን...

ሁሉም ባንኮች አዲስ እና ነባር ሂሳቦችን ለማስተሳሰር ወደ VeriFayda 2 እንዲሸጋገሩ ተወሰነ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እና የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም፣ የፋይዳ ዲጂታል...

NBE orders financial institutions to link accounts with Fayda ID

The National Bank of Ethiopia (NBE) has ordered all...

TECNO’s AFCON-Ready AI Features Reflect a New Era in Mobile Sports Viewing

#Advertorial TECNO, official CAF global partner, introduces four intelligent tools...

Instant Payments, Big Data & High Availability: Why Banks in Ethiopia Need a Robust Data Backbone

By Demos Kyriacou Instant payments, big data and high availability...
spot_img

Related Articles

Popular Categories

spot_imgspot_img