Friday, April 17, 2026

አይኤምኤፍ ለኢትዮጵያ 261 ሚሊዮን ዶላር እንዲለቀቅ የባለሞያዎች ደረጃ ስምምነት ላይ ደረሰ

ዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (አይኤምኤፍ) ከኢትዮጵያ ጋር በ3.4 ቢሊዮን ዶላር የተራዘመ የብድር ፋሲሊቲ መርሃግብር በአራተኛው ግምገማ ላይ በባለሞያዎች ደረጃ ስምምነት ላይ መድረሱን አስታውቋል።

ይህ ስምምነት የአይኤምኤፍ ሥራ አስፈፃሚ ቦርድ ሲያጸድቀው፣ ቀጣዩ የ261 ሚሊዮን ዶላር ክፍያ ለኢትዮጵያ እንዲለቀቅ መንገድ ይከፍታል። ይህ ክፍያ ሲፈጸም በአጠቃላይ በፕሮግራሙ ስር ለኢትዮጵያ የተሰጠው የገንዘብ ድጋፍ ወደ 2.13 ቢሊዮን ዶላር ከፍ ይላል።

የገንዘብ ተቋሙ ባወጣው መግለጫ፣ የኢትዮጵያ መንግሥት የጀመረውን የማክሮ ኢኮኖሚ ማረጋጋት እና የልማት ማሻሻያዎችን በመገምገም፣ “የተሃድሶውን ፍጥነት ማስቀጠል የማክሮ ኢኮኖሚ መረጋጋትን ለማጠናከር እና በመካከለኛ ጊዜ ዕድገትንና ድህነትን ለመቀነስ ቁልፍ ይሆናል” የሚል አስተያየት ሰጥቷል።

ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ በሐምሌ 2024 የድጋፍ ብድሩን ስትይዝ፣ ከባድ የውጭ ዕዳ መልሶ የማዋቀር ሥራ ላይ ትገኛለች። አይኤምኤፍ ባወጣው ሪፖርት፣ በG20 የጋራ ማዕቀፍ ስር የዕዳ ዘላቂነትን ለመመለስ የሚደረጉ ጥረቶች እየገፉ መሆናቸውን ጠቁሟል።

ምንም እንኳን ኢትዮጵያ ከሁለትዮሽ አበዳሪዎች ጋር በመደበኛ ዕዳዋ ላይ ስምምነት ላይ ብትደርስም፣ ባለሀብቶች ከ1 ቢሊዮን ዶላር የዩሮቦንድ ጋር በተያያዘ በሚደረገው የዕዳ ቅናሽ መጠን ላይ አለመግባባት መኖሩ የሂደቱን መጓተት እንዳስከተለ ይታወቃል።

በአይኤምኤፍ የባለሞያዎች ቡድን መሪ በሆኑት በአልቫሮ ፒሪስ የሚመራው ቡድን ከጥቅምት 20 እስከ ህዳር 4 ቀን 2018 ዓ.ም. ድረስ በአዲስ አበባ በመገኘት፣ በአይኤምኤፍ የተራዘመ የብድር ፋሲሊቲ መርሃግብር ስር በአራተኛው ግምገማ ዙሪያ ውይይት ማድረጋቸው ይታወቃል። ይህ ተከትሎ ደግሞ ከህዳር 24 እስከ 26 ቀን 2018 ዓ.ም. የቀጠለው ዉይይት በአዲስ አበባ ተካሄዶ ነበር።

ሚስተር ፒሪስ እንደተናገሩት ፤ ​“የአይኤምኤፍ ባለሞያዎች ቡድን እና የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት በተራዘመ የብድር ፋሲሊቲ ስምምነት ስር በኢትዮጵያ ኢኮኖሚያዊ ፕሮግራም በአራተኛው ግምገማ ላይ በባለሞያዎች ደረጃ ስምምነት ላይ ደርሰዋል። ስምምነቱ በሚቀጥሉት ሳምንታት የአይኤምኤፍ ማኔጅመንት እና ሥራ አስፈፃሚ ቦርድ ማጽደቅ ይጠበቅበታል።

የማሻሻያውን ፍጥነት ማስቀጠል የማክሮ ኢኮኖሚ መረጋጋትን ለማጠናከር እና በመካከለኛ ጊዜ ዕድገትንና ድህነትን ለመቀነስ ቁልፍ ይሆናል ያሉት አልቫሮ የዋጋ ግሽበትን ለመግታት ጥብቅ የገንዘብ ፖሊሲ መከተል ተገቢ እንደሆነ አፅንኦ ሰጥተዉ ተናግረዋል ።

የባለሞያዎች ቡድን ከአስተዳዳሪዎች ጋር ባለፈዉ ሳምንት በኢትዮጵያ በነበራቸዉ ቆይታ ከገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሽዴ፣ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ እዮብ ተካለኝ እና ሌሎች ከፍተኛ ባለሥልጣናት ጋር ተገናኝቶ ውይይት ማድረጋቸው ይታወሳል።

Hot this week

Production up, but the ‘cost’ variable weighs heavily

Production is up in 2021 for the Italian agricultural...

Luminos Fund’s catch-up education programs in Ethiopia recognized

The Luminos Fund has been named a top 10...

Well-planned cities essential for a resilient future in Africa concludes the World Urban Forum

The World Urban Forum (WUF) concluded today with a...

Private sector deemed key to unlocking AfCFTA potential

The private sector’s role is vital to fully unlock...

Z Library and the Global Spread of Educational Resources

Access to knowledge once moved at the pace of...

Renowned artist and educator Behailu Bezabih passes at 66

Ethiopia’s art community is mourning the loss of Behailu...

Black Sea imports outpace local supply as Ethiopia battles tight grain markets

Ethiopia’s agricultural sector is navigating a complex paradox of...

Afri Fund Capital eyes $6 billion raise for Lapsset project

Nairobi -based Afri Fund Capital has announced an ambitious...

Sudan and Ethiopia agree to boost air connectivity

Sudan and Ethiopia have moved to renew civil aviation...

AI is fuelling the ‘Digital Colonisation’ of Africa, warns UN Scientist

The United Nations has launched its first global panel...

Parliament approves law allowing companies, NGOs to provide farm services

The House of Peoples’ Representatives has cleared a law...

Ringleader of suspected human trafficking network arrested in Ethiopia

Police have arrested a man accused of being at...
spot_img

Related Articles

Popular Categories

spot_imgspot_img