Thursday, February 5, 2026

የውጭ ትምህርት ቤቶች 30% ከሀገራቸው መንግሥት ድጋፍ ማረጋገጫ እንዲያቀርቡ የሚያስገድድ ረቂቅ ደንብ ይፋ አደረገ

​ትምህርት ሚኒስቴር በኢትዮጵያ ውስጥ የሚንቀሳቀሱ መንግሥታዊ ያልሆኑ የትምህርት ተቋማት የሚመሩበትን አዲስ ረቂቅ ደንብ ማዘጋጀቱን ያስታወቀ ሲሆን፣ ረቂቁ በተለይ በውጭ ሀገር ማኅበረሰቦች ለሚቋቋሙ ትምህርት ቤቶች አስገዳጅ መስፈርቶችን አኑሯል።

ካፒታል የተመለከተዉ ​ረቂቅ ደንቡ እንደሚያስገድደው፣ በውጭ ሀገር ማኅበረሰብ የተቋቋሙ ትምህርት ቤቶች ከጠቅላላ በጀታቸው ውስጥ 30% (ሰላሳ በመቶ) የሚሆነው ከሀገራቸው መንግሥት ድጋፍ ማግኘታቸውን የሚያረጋግጥ ሰነድ ማቅረብ ይኖርባቸዋል። ቀሪውን 70% ደግሞ ራሳቸው መሸፈን የሚችሉ መሆናቸውን የሚያሳይ ማረጋገጫ እንዲያቀርቡ ግዴታ ተጥሏል።

​ይህ የፋይናንስ ማረጋገጫ በኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርና አግባብ ባለው የሰነዶች ማረጋገጫ ባለሥልጣን ተረጋግጦ መቅረብ እንዳለበት ደንቡ ያመለክታል። ሚኒስቴሩ ይህን መስፈርት ያኖረው በኢትዮጵያ ውስጥ የሚንቀሳቀሱ ዓለም አቀፍ ትምህርት ቤቶች የፋይናንስ መረጋጋትና አስተማማኝነት ለማረጋገጥ ያለመ እንደሆነ ይጠበቃል።

በዚህ ለትምህርት ማህበረሰቡና ባለድርሻ አካላት አስተያየት ክፍት በተደረገዉ አዱሱ ረቂቅ ደንብ፤ መንግሥታዊ ያልሆኑ የትምህርት ተቋማት የአገሪቱን የትምህርት ሕግ፣ የመምህራን ብቃት፣ የተማሪዎች መብት እና የትምህርት ደረጃን ጨምሮ ሌሎች ተያያዥ ሕጎችን ማክበር ይጠበቅባቸዋል።

በዚህ ደንብ ላይ እንደተገለፀዉ ፤​ተቋማቱ የራሳቸው የሆነ የገንዘብ ምንጭ (ከተማሪዎች ክፍያ፣ ከስጦታ ወይም ከኢንቨስትመንት ትርፍ) እና ነጻ አስተዳደር ያለው ድርጅታዊ አወቃቀር ሊኖራቸው ይገባል።

​ረቂቅ ደንብ ላይ ሚኒስቴሩ ተቋማት ሊያስከፍሉት የሚችሉትን የትምህርትና ሌሎች አገልግሎት ክፍያዎችን ጣሪያ በተመለከተ መመሪያ እንደሚያወጣና በየሦስት ዓመቱ እንደሚስተካከል ደንግጓል። የክፍያ ጭማሪ ለማድረግ ከ3 ወራት በፊት ተጠቃሚዎችን ማወያየት እንደሚኖርባቸው ያስገድዳል።

​መንግሥታዊ ያልሆኑ የአጠቃላይ ትምህርት ተቋማት ሚኒስቴሩ በሚያወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት እንደገና መመዝገብ እንዳለባቸው የተገለፀ ሲሆን ተቋማት የልዩ ፍላጎት ላላቸው ተማሪዎች ምቹ ሁኔታን መፍጠር እና ተማሪዎቻቸው ከአንደኛ ክፍል ጀምሮ የትምህርት የምክር አገልግሎት ማግኘታቸውን ማረጋገጥ እንዳለባቸው አስታዉቋል።

ትምህርት ሚኒስትሩ ​አዲሱ ደንብ የመንግሥታዊ ያልሆኑ ትምህርት ተቋማትን ምዝገባ፣ ዕውቅና እና ቁጥጥር በአጠቃላይ ትምህርት አዋጅ ቁጥር 1368/2017 መሠረት የሚያከናውን መሆኑን በግልጽ አስረድቷል።

Hot this week

Production up, but the ‘cost’ variable weighs heavily

Production is up in 2021 for the Italian agricultural...

Luminos Fund’s catch-up education programs in Ethiopia recognized

The Luminos Fund has been named a top 10...

Well-planned cities essential for a resilient future in Africa concludes the World Urban Forum

The World Urban Forum (WUF) concluded today with a...

Private sector deemed key to unlocking AfCFTA potential

The private sector’s role is vital to fully unlock...

ዮሐንስ አያሌው (ዶ/ር) የፀደይ ባንክ ፕሬዝዳንት ለመሆን ከስምምነት መድረሳቸው ተገለጸ

የአማራ ባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ በመሆን ሲያገለግሉ የቆዩት ዮሐንስ...

በአንድ ሳምንት ልዩነት የዶላር ዋጋ ጭማሪ አሳየ፤ ከፍተኛው መግዣ 155.05 ብር ደረሰ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በሕገ-ወጥ የውጭ ምንዛሬ ገበያ ላይ የታየውን...

መንግሥት በነዳጅ ላይ ሲያደርግ የነበረውን ድጎማ እስከ መጪው የካቲት ወር ሙሉ በሙሉ ሊያነሳ ነው

መንግሥት ላለፉት አራት ዓመታት በነዳጅ ምርቶች ላይ ሲያደርግ የነበረውን...

Six African cities take stock of fiscal reforms in drive toward sustainable urban finance

City leaders and finance officials from across the continent...

KOICA strengthens WFP’s efforts to prevent malnutrition in Ethiopia

The United Nations World Food Programme (WFP) has welcomed a...
spot_img

Related Articles

Popular Categories

spot_imgspot_img