Sunday, July 26, 2026

ፍርድ ቤቱ በኢትዮጵያና በአዲስ አበባ ንግድ ምክር ቤቶች ሕንፃ ውዝግብ ላይ የእግድ ውሳኔ አስተላለፈ

በኢትዮጵያ ንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት (ኢትዮጵያ ቻምበር) እና በአዲስ አበባ የንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት (አዲስ ቻምበር) መካከል በሜክሲኮ አደባባይ በሚገኘው የንግድ ምክር ቤቶች ሕንፃ ላይ በቀረበው የይገባኛል ውዝግብ ላይ፣ የቂርቆስ ምድብ 1ኛ ፍ/ብሄር ችሎት የእግድ ዉሳኔ አስተላልፏል።

ፍርድ ቤቱ በዛሬው እለት በሰጠው ውሳኔ መሰረት፣ ኢትዮጵያ ቻምበር ቀደም ሲል ይዞ የነበረውን የቢሮ ክፍል በአስቸኳይ ለአዲስ ቻምበር እንዲያስረክብ ጥብቅ ትዕዛዝ ሰጥቷል።

ፍርድ ቤቱ ይህን ውሳኔ የሰጠው፣ ኢትዮጵያ ቻምበር ቀደም ሲል የፍርድ ቤቱን ብይን በመጣስ፣ አዲስ ቻምበር ይዟቸው የነበሩ ክፍሎችን በኃይል እንደያዘ አዲስ ቻምበር ባቀረበው አቤቱታ መሰረት ነው።

ፍርድ ቤቱ ህዳር 1 ቀን 2018 ዓ.ም. ባሳለፈው ብይን፣ ተከሳሽ (ኢትዮጵያ ቻምበር) ሕንጻውን ለልማት ከማዋሉ በፊት ለአዲስ ቻምበር ምትክ ክፍሎችን አስቀድሞ ማዘጋጀትና ለፍርድ ቤቱ ማሳወቅ እንደነበረበት አመልክቶ ነበር።

የኢትዮጵያ ቻምበር ይህንን ትዕዛዝ በመጣስ የክፍሎቹን ቁልፎች ሰብሮ መግባቱ በአዲስ ቻምበር በኩል መገለጹን ተከትሎ፣ ፍርድ ቤቱ ኢትዮጵያ ቻምበር ክፍሎቹን በአስቸኳይ ለከሳሽ (አዲስ ቻምበር) እንዲያስረክብ በድጋሚ በጥብቅ አዟል።

የካፒታል ዘገባ የዓይን እማኞችን ዋቢ አድርጎ እንደዘገበው፣ ቁጥራቸው 20 ገደማ የሆኑ የኢትዮጵያ ቻምበር ሰራተኞች የቢሮውን ግድግዳና በር በመስበር ንብረቶችን ወደ ውጪ ሲጥሉ ነበር።

የኢትዮጵያ ንግድና ዘርፍ ማኅበራት ምክር ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ሰብስብ አባፊራ በበኩላቸው፣ “በፍርድ ቤቱ ተጥሎ የነበረውን የማልማት እግድ ትላንት (ህዳር 1 ቀን 2018 ዓ.ም.) በማንሳቱ ነው ዛሬ (ህዳር 2 ቀን 2018) ወደ ተግባር የገባነው” ሲሉ ለካፒታል ገልፀው ነበር። የንግድ ምክር ቤቶች ሕንፃ ውዝግብ ወደ አዲስ ምዕራፍ መሸጋገሩን የፍርድ ቤቱ ውሳኔ ያመለክታል።

Hot this week

Production up, but the ‘cost’ variable weighs heavily

Production is up in 2021 for the Italian agricultural...

Luminos Fund’s catch-up education programs in Ethiopia recognized

The Luminos Fund has been named a top 10...

Well-planned cities essential for a resilient future in Africa concludes the World Urban Forum

The World Urban Forum (WUF) concluded today with a...

Private sector deemed key to unlocking AfCFTA potential

The private sector’s role is vital to fully unlock...

Ethiopia’s digital finance sector gets new trade body

Ethiopia’s digital finance industry has entered a new phase...

Ethio Telecom, Netflix in talks over Ethiopia expansion

Ethio telecom says it is in ongoing discussions with...

The Glitter and the Gaps: Reflections of a Returnee on Ethiopia’s Uneven Transformation

After twenty‑eight years away, I returned home with equal...

Yared Alemayehu

2. Education: (የት/ት ደረጃ)    BA in Education3. Company name: (የመስሪያ...

“Aspiration beyond government paycheck’’

Civil Servant Voice - Unheard  On September 11, 2026, the...

Beyond the Binary: Navigating Epistemology, Modernity, and the Search for True Spirituality

The Ethiopian struggle between tradition and modernity did not...

Talent grammar and the frame of judgment

Certain vocal techniques, genres, and performance conventions can be...
spot_img

Related Articles

Popular Categories

spot_imgspot_img