Saturday, November 15, 2025

በትግራይ የካናዳ ኩባንያ ማዕድን ቦታዎች ላይ ህገወጥ የማዕድን ቁፋሮ ተጧጡፏል ሲል አዲስ ጥናት አመለከተ

በኢያሱ ዘካርያስ

በትግራይ ክልል ውስጥ ከሁለት ዓመታት የእርስ በርስ ግጭት በኋላ፣ በዓለም አቀፍ ላይ የሚስተዋለዉን የወርቅ ዋጋ መናር ተከትሎ በቢሊዮን የሚቆጠር ዶላር የሚያንቀሳቅስ ሕገ-ወጥ የወርቅ ንግድ መፋፋሙን አዲስ የጋራ ምርመራ አመለከተ።

ምርመራው እንደሚያመለክተው፣ የካናዳው ኩባንያ ኢስት አፍሪካ ሜታልስ ንብረት በሆኑት ማቶ ቡላ እና ዳ ታምቡክ ማዕድን ቦታዎች ላይ ሕገወጥ የማዕድን ማውጣት ተግባር በስፋት እየተፈጸመ ነው።

ዘ ግሎብ ኤንድ ሜይል ከ ቡሮ ኦፍ ኢንቨስቲጌቲቭ ጆርናሊዝም ጋር ባደረጉት ምርመራ መሠረት፣ ሥራ ያልጀመሩና ተደራሽ አይደሉም የተባሉት እነዚህ ቦታዎች ላይ፣ የቀድሞ ወታደሮች እና የቻይና ማዕድን ቆፋሪዎች ስማቸው ያልተገለጸ ባለሀብቶች ድጋፍ አግኝተው ከ2024 መጀመሪያ አንስቶ እስከ 2025 አጋማሽ ድረስ ወርቅ ሲያወጡ ቆይተዋል።

ሪፖርቱ በክልሉ ከጦርነቱ በኋላ በተፈጠረው የፖለቲካ ክፍተት ሳቢያ ያልተገደበ የማዕድን ማውጣት ኢኮኖሚ መጧጧፉን ያሳያል። ወታደራዊ ቡድኖች እና የአካባቢ አዛዦች ቁልፍ የማዕድን ክምችቶችንና የኮንትሮባንድ መንገዶችን በመቆጣጠር፣ ሕገወጥ ቁፋሮው እንዲስፋፋና የክልሉ ሀብት በቁጥጥር ስር በሌለ መንገድ እንዲባክን ምክንያት ሆነዋል።

የወርቅ ዋጋ በዓለም ገበያ በዚህ ዓመት ብቻ ከ50% በላይ መጨመሩ ዋናው ማነቃቂያ ሲሆን፣ ክልሉ የአካባቢው ማህበረሰብ ተጠቃሚነት ሳይረጋገጥ ወደ “ሱዳን መሰል የሀብት ግጭት” ሊያመራ የሚችል አደጋ ተጋርጦበታል ተብሏል።

የቀድሞ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ ፕሬዝዳንት የነበሩት አቶ ጌታቸው ረዳ ሕገወጥ ተግባሩን ለማስቆም እና ንብረቶችን ለመያዝ ግብረ ኃይል ቢሰማሩም፣ በደቡባዊው የክልሉ ክፍል እየተባባሰ ያለው ግጭት የማስፈጸም ስራውን አደጋ ላይ እየጣለው መሆኑ ተገልጿል።

በ2017 በጀት ዓመት 10 ወራት ብቻ ከትግራይ ክልል ለብሔራዊ ባንክ ከ12 ሺህ 210 ኪሎ ግራም በላይ ወርቅ ገቢ የተደረገ ሲሆን፣ ይህም ከሌሎች ክልሎች የሚበልጥ ሆኖ መመዝገቡ ይታወሳል።

የቫንኩቨሩ ኩባንያ ኢስት አፍሪካ ሜታልስ፣ ሁለቱን ፕሮጀክቶች ለማልማት ከቻይናው ቲቤት ሁዋዩ ማይኒንግ ጋር እንደሚሰራ አስታውቋል። የቻይናው አጋር ፕሮጀክቶቹ ሙሉ ፍቃድ ያላቸው መሆናቸውንና ለምርት ዝግጁ እስኪሆኑ ድረስ 100% የልማት ወጪዎችን እንደሚሸፍን ኩባንያው ገልጿል።

ይሁን እንጂ፣ ኢስት አፍሪካ ሜታልስ በየትኛውም ሕገወጥ ተግባር ውስጥ እንዳልተሳተፈ በመግለጽ፣ የቻይና አጋሮቹም ሕገወጥ ቁፋሮዎችን ፈጽመዋል የሚለውን ክስ ውድቅ አድርጓል። ሆኖም ባለሙያዎች እንደሚሉት፣ ከሲልክ ሮድ ኢንቨስትመንትስ እና ከትግራይ ሪሶርስስ ጋር ግንኙነት ያላቸው የቻይና ቡድኖች በእነዚህ ቦታዎች ላይ ወርቅ ሲያወጡ መቆየታቸውን አመልክተዋል።

Hot this week

Production up, but the ‘cost’ variable weighs heavily

Production is up in 2021 for the Italian agricultural...

Luminos Fund’s catch-up education programs in Ethiopia recognized

The Luminos Fund has been named a top 10...

Well-planned cities essential for a resilient future in Africa concludes the World Urban Forum

The World Urban Forum (WUF) concluded today with a...

Private sector deemed key to unlocking AfCFTA potential

The private sector’s role is vital to fully unlock...

ኢትዮጵያ አየር መንገድ እና ፍላይዱባይ የሶማሊያ ኢ-ቪዛ ለሶማሊላንድ በረራዎች እንደማይሠራ አረጋገጡ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ እና ፍላይዱባይ (FlyDubai) ወደ ሶማሊላንድ ለሚደረጉ...

Elephant Bet Ethiopia Backs Local Football Growth in Dire Dawa

The city of Dire Dawa has turned into one...

የአፍሪካ ኅብረት ዕዳን ለመቋቋም “አዲስ የፋይናንስ ስምምነት” እና ፍትሐዊ የክፍያ ሁኔታዎችን ጠየቀ

የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ማህሙድ አሊ ዩሱፍ፤ አህጉሪቱ ከዓለም...

የውጭ ትምህርት ቤቶች 30% ከሀገራቸው መንግሥት ድጋፍ ማረጋገጫ እንዲያቀርቡ የሚያስገድድ ረቂቅ ደንብ ይፋ አደረገ

​ትምህርት ሚኒስቴር በኢትዮጵያ ውስጥ የሚንቀሳቀሱ መንግሥታዊ ያልሆኑ የትምህርት ተቋማት...

ፍርድ ቤቱ በኢትዮጵያና በአዲስ አበባ ንግድ ምክር ቤቶች ሕንፃ ውዝግብ ላይ የእግድ ውሳኔ አስተላለፈ

በኢትዮጵያ ንግድና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት (ኢትዮጵያ ቻምበር) እና...

Re: CALL FOR EXTERNAL AUDIT SERVICES

Initiative Africa (IA), an Ethiopian Resident Charity dedicated to...

Invitation To Tender

For the supply of Vegetable seed Tender Reference -...
spot_img

Related Articles

Popular Categories

spot_imgspot_img