Monday, September 14, 2026

ፒተር ንዴግዋን የተኩት ኤርሚያስ እሸቱ የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ቦርድን ሊመሩ ነው

ሳፋሪኮም ቴሌኮሙኒኬሽንስ ኢትዮጵያ ኃ.የተ.የግ.ማ.፣ የኩባንያውን የአድቫይዘሪ ቦርድ ሊቀመንበርነት ቦታ ለአዲስ መሪ መስጠቱን አስታውቋል። የግሎባል ፓርትነርሺፕ ፎር ኢትዮጵያ (GPE) ቦርድ አቶ ኤርሚያስ እሸቱን ቀደም ሲል የቦርዱን ሊቀመንበርነት ሲመሩ የነበሩትን ፒተር ንዴግዋን በመተካት፣ ከህዳር 1 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የአድቫይዘሪ ቦርድ ሊቀመንበር አድርጎ ሾሟል።

ይህ ሹመት ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ለአካባቢያዊ አመራር (localization) እና ለኢትዮጵያውያን በከፍተኛ የአመራር ሚናዎች ውስጥ ተሳትፎ እንዲኖራቸው ለሚያደርገው ጥረት ትልቅ ምዕራፍ እንደሆነ ተገልጿል።

አቶ ኤርሚያስ ከመጋቢት 12 ቀን 2017 ዓ.ም. ጀምሮ የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የአድቫይዘሪ ቦርድን የተቀላቀሉ የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ አባል ነበሩ። አሁን ወደ ሊቀመንበርነት ማደጋቸው የኩባንያው በአገር ውስጥ አመራር ላይ ያለውን እምነት ያጎላል ተብሏል።

በአዲሱ ኃላፊነታቸውም ቦርዱ ውጤታማ ሆኖ እንዲሠራ መምራትና ማስተባበር፣ እንዲሁም ኩባንያውን በውጭ ግንኙነት መወከል ይጠበቅባቸዋል።

የGPE ቦርድ ሊቀመንበር እና የሳፋሪኮም ኃ.የተ.የግ.ማ. ዋና ስራ አስፈጻሚ የሆኑት ፒተር ንዴግዋ በሰጡት አስተያየት፡- “የእርሳቸው (የኤርሚያስ) በፋይናንስ፣ በአስተዳደር እና በተቋማዊ ለውጥ ላይ ያለው ሰፊ ልምድ፣ ከገበያው ጥልቅ ግንዛቤ ጋር ተዳምሮ ኩባንያውን ወደ ቀጣዩ የዕድገት ምዕራፍ ለመምራት ያስችላቸዋል።” ብለዋል

ፒተር ንዴግዋ ከመጋቢት 2017 ዓ.ም. ጀምሮ የግሎባል ፓርትነርሺፕ ፎር ኢትዮጵያ ቦርድ እና የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የአድቫይዘሪ ቦርድ ሊቀመንበር ሆነው ሲያገለግሉ የቆዩ ሲሆን፣ አሁን ግን በGPE ቦርድ ሊቀመንበርነት ብቻ ይቀጥላሉ።

GPE ቦርድ ብሪቲሽ ኢንተርናሽናል ኢንቨስትመንት፣ ኢንተርናሽናል ፋይናንስ ኮርፖሬሽን፣ ቮዳኮም፣ ቮዳፎን፣ ሳፋሪኮም ኃ.የተ.የግ.ማ. እና ሱሚቶሞ ኮርፖሬሽን የተሰኙ ዓለም አቀፍ ተቋማትን ያካትታል።

አቶ ኤርሚያስ እሸቱ የኢትዮጵያን የኢኮኖሚ ዘመናዊነት እና የግል ዘርፍ ዕድገት በማስፋፋት የሚታወቁ፣ በንግድ አስተዳደር፣ በፋይናንስ እና በቴክኖሎጂ ዘርፎች ከ25 ዓመታት በላይ ልምድ ያካበቱ መሪ መሆናቸው ተመላክቷል።

ቀደም ሲል የኢትዮጵያ ምርት ገበያ (ECX) ዋና ስራ አስፈጻሚ በመሆን የኢትዮጵያን የመጀመሪያውን የኤሌክትሮኒክስ ግብይት መድረክ የጀመሩ ሲሆን፣ ዘመን ባንክን ከመሰረቱት እና በኋላም ሊቀመንበር ከሆኑት መካከል አንዱ ናቸው።

በአቶ ኤርሚያስ አመራር ስር የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ቦርድ ህግ አስተዳደርን በማጠናከር፣ የስራ ዕድል በመፍጠር እና ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የድርጅት አሰራርን በመትከል በኢትዮጵያ አሳታፊ ዲጂታል-ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ለማምጣት ትኩረት እንደሚያደርግ ተጠቁሟል።

Hot this week

Production up, but the ‘cost’ variable weighs heavily

Production is up in 2021 for the Italian agricultural...

Luminos Fund’s catch-up education programs in Ethiopia recognized

The Luminos Fund has been named a top 10...

Well-planned cities essential for a resilient future in Africa concludes the World Urban Forum

The World Urban Forum (WUF) concluded today with a...

Private sector deemed key to unlocking AfCFTA potential

The private sector’s role is vital to fully unlock...

Safaricom surpasses 15 million subscribers as it marks five years

Safaricom is marking five years since it received a...

Africa’s economic momentum is building as savings and cross-border trade activity accelerate

Rising savings, increasing cross-border payment activity and growing participation...

Experts urge sovereign AI models tailored to African realities

Researchers and leaders across Africa have been urged to...

Addis Ababa deploys digital monitoring Apps to track urban air quality

The Addis Ababa Transport Bureau has announced the deployment...

BRICS at 20: Diverse Strengths, Shared Growth

By Liu Yuanhui, CGTN The Driver's Cabin What do 20 years...

Ethiopia Boosts Drone Production to Fight Rebels

Ethiopia has been manufacturing drones at two factories since...

Hijacking Pirates Exploit Regional Chaos to Return to Seas off Somalia

The scourge of Somali piracy targeting cargo ships and...
spot_img

Related Articles

Popular Categories

spot_imgspot_img