Sunday, September 20, 2026

የወጪ ንግድ ኮንትራት ምዝገባና የመላኪያ ፈቃድ አገልግሎት ከመጪው ሰኞ ጀምሮ በኦላይን ሊሆን ነዉ

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ለንግዱ ማኅበረሰብ የሚሰጠውን የሁለት ወሳኝ አገልግሎቶችን ማለትም የወጪ ንግድ ኮንትራት ምዝገባ እና የመላኪያ ፈቃድ አገልግሎት ከመጪዉ ሰኞ ከታህሳስ 06 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ ሙሉ በሙሉ ወደ ኦንላይን (በበይነ መረብ) ሥርዓት ማዘመኑን አስታወቀ።

የንግድ ስርዓትና ላይሰንሲንግ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ የሆኑት አብዱልሀኪም ሙሉ እንዳስታወቁት፣ ይህ እርምጃ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ለንግዱ ማኅበረሰብ የሚያቀርባቸውን አገልግሎቶች በቴክኖሎጂ በማዘመን ረገድ የወሰደው ሌላ ወሳኝ ምዕራፍ ነው።

ቀደም ሲል በማኑዋል ሲሰጥ የነበረው ይህ አገልግሎት ወደ ኦንላይን ሥርዓት ሙሉ በሙሉ መሸጋገሩ የአገልግሎቱን ተደራሽነት ከፍ ያደርጋል ተብሏል።

አብዱልሀኪም እንዳብራሩት፣ ይህ አዲስ የተዘረጋው ሥርዓት ላኪዎች የሚፈልጉትን አገልግሎት ከሰው ንክኪ ነጻ በሆነ መልኩ ባሉበት ቦታ ሆነው እንዲያገኙ ያስችላል። ይህም የተገልጋዮችን ጊዜና ወጪ ከመቆጠብም በላይ አገልግሎቱን ዘመናዊና ፍትሐዊ ያደርገዋል።

ሚኒስትር ዴኤታው አክለውም መንግስት የተገልጋዮችን እርካታ ለማረጋገጥ መጠነ ሰፊ ማሻሻያዎችን እያደረገ መሆኑን ገልጸው፣ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የሚሰጣቸውን አገልግሎቶች ቴክኖሎጂን መሰረት ያደረጉና ወጪ ቆጣቢ እንዲሆኑ በትጋት እየሰራ መሆኑን አስረድተዋል።

ይህን ተከትሎ የንግድ ለመጀመር ይወስድ የነበረው ጊዜ ከ32 ቀናት ወደ 5 ቀን ወርዷል የተባለ ሲሆን ለንግድ ሥራ አጀማመር ይወስድ የነበረው ሂደት ደግሞ ከ11 ደረጃዎች ወደ 4 ደረጃዎች ዝቅ ማድረግ መቻሉን ካፒታል ያገኘው መረጃ ያመለክታል።

Hot this week

Production up, but the ‘cost’ variable weighs heavily

Production is up in 2021 for the Italian agricultural...

Luminos Fund’s catch-up education programs in Ethiopia recognized

The Luminos Fund has been named a top 10...

Well-planned cities essential for a resilient future in Africa concludes the World Urban Forum

The World Urban Forum (WUF) concluded today with a...

Private sector deemed key to unlocking AfCFTA potential

The private sector’s role is vital to fully unlock...

Abel Birhanu

2. Education: (የት/ት ደረጃ)    10th 3. Company name: (የመስሪያ ቤቱ ስም)    Abel...

Ethiopia unveils 10-year master plan to transform date palm into major export crop

Ethiopia is orchestrating a structural transformation across its agricultural...

Africa at BRICS New Delhi: what it contributed and what it gained

The successful conclusion of the 18th BRICS Summit in...

Clearing the haze

Addis Ababa is confronting a severe environmental challenge, as...

Sub-Saharan Africa faces digital divide as handset costs and usage gap persist

While global mobile broadband networks continue to expand, Sub-Saharan...

El Niño drought threatens Ethiopian power supply to crypto miners

Ethiopian Electric Power (EEP) has confirmed that it may...
spot_img

Related Articles

Popular Categories

spot_imgspot_img