Sunday, April 26, 2026

የሐበሻ ቢራ ፋብሪካ በ40% ኤክሳይዝ ታክስ ምክንያት ሊመጣ የሚችለውን ከባድ ተጽዕኖ አስጠነቀቀ

በኢትዮጵያ ቀዳሚ ከሆኑት የቢራ አምራቾች አንዱ የሆነው የሐበሻ ቢራ አክሲዮን ማኅበር፣ በኢንዱስትሪው ላይ የተጣለው የ40% ኤክሳይዝ ታክስ እና አዲሱ የዲጂታል ኤክሳይዝ ታክስ ስታምፕ አሠራር በኩባንያው የፋይናንስና የሥራ እንቅስቃሴ ላይ ከፍተኛ ጫና እያሳደረ መሆኑን አስጠነቀቀ።

ኩባንያው እንደሚገልጸው፣ ይህ 40 በመቶ የታክስ ተመን ታክሱ ምርቱ ከፋብሪካ ቅጥር ግቢ በወጣ ቅጽበት የሚታሰብና የሚከፈል በመሆኑ፣ ተቋሙ ገና ምርቱን ለገበያ አቅርቦ ገቢ ሳያገኝ ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ ለመንግሥት እንዲያስረክብ ይገደዳል።

ይህ አሠራር በተለይ እንደ ሐበሻ ቢራ ላሉ በማስፋፊያና በከፍተኛ የሥራ ማስኬጃ ወጪ ውስጥ ላሉ ኩባንያዎች ትልቅ የፋይናንስ ጫና ፈጥሯል።

ከነባሩ የታክስ ጫና በተጨማሪ፣ መንግሥት የንግድ ቁጥጥርን ለማጥበቅ ያስተዋወቀው የዲጂታል ኤክሳይዝ ታክስ ስታምፕ ሥርዓት ለኢንዱስትሪው ሌላው ትልቅ ስጋት ሆኗል። ሐበሻ ቢራ እንደገለፀው ፤ ይህ ሥርዓት በሚቀጥሉት አምስት ዓመታት ውስጥ ብቻ ወደ 372.3 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር የሚጠጋ ቀጥተኛ ወጪ ያስከትላል።

ከዚህ የገንዘብ መጠን ውስጥ 223 ሚሊዮን ዶላር የሚሆነው ለሥራ ማስኬጃ የሚውል ሲሆን፣ ይህም በአገሪቱ እጥረት ባለበትና በከፍተኛ ሁኔታ በሚፈለገው የውጭ ምንዛሬ የሚከፈል ነው።

ይህ ወጪ በምርቱ የመሸጫ ዋጋ ላይ የሚኖረው ተጽዕኖ በቀላሉ የሚታይ አይደለም። “ይህ ሥርዓት የታክስ አሰባሰብን ለማዘመን የታለመ ቢሆንም፣ የሚጠይቀው ወጪ ግን የኢንዱስትሪውን አቅም የሚፈታተን ነው” ይላሉ የዘርፉ ባለሙያዎች።

የቢራ ኢንዱስትሪው ከኢኮኖሚያዊ ተጽዕኖዎች በተጨማሪ ማኅበራዊና ፖለቲካዊ ጫናዎችም እየበረቱበት ይገኛሉ። በቅርብ ዓመታት ውስጥ በአልኮል መጠጥ ላይ የሚሰነዘሩ ትችቶች መጨመራቸው መንግሥት ጥብቅ ገዳቢ እርምጃዎችን እንዲወስድ አድርጎታል።

በመገናኛ ብዙኃንና በሕዝባዊ ቦታዎች ላይ የተጣለው የአልኮል ማስታወቂያ እገዳ፣ ኩባንያዎች አዳዲስ ምርቶቻቸውን ለደንበኞቻቸው እንዳያስተዋውቁና የምርት ስማቸውን (Brand) እንዳይገነቡ አግዷቸዋል።

ይህ እገዳ ኩባንያዎች ደንበኞቻቸውን ለማግኘት ይበልጥ ውድ የሆኑና አድካሚ የሆኑ የንግድ ማስተዋወቂያ ስልቶችን እንዲከተሉ አስገድዷቸዋል፣ ይህም ተጨማሪ ወጪን የሚጠይቅ ነው።

ኩባንያው የገበያ ተደራሽነቱን ለማስፋት በሚያደርገው ጥረት ውስጥ እንቅፋቶች እንዳሉበት የገለፀ ሲሆን እነሱም እንደ ጠላ፣ ጠጅ እና አረቄ ያሉ ባሕላዊ መጠጦች ናቸው። እነዚህ መጠጦች ምንም ዓይነት የኤክሳይዝ ታክስ የማይከፈልባቸውና በዝቅተኛ ዋጋ በየመንደሩ የሚገኙ በመሆናቸው፣ የታክስ ጫና ያለበትን የፋብሪካ ቢራ በዋጋ እንደሚገዳደሩት አስታውቋል።

Hot this week

Production up, but the ‘cost’ variable weighs heavily

Production is up in 2021 for the Italian agricultural...

Luminos Fund’s catch-up education programs in Ethiopia recognized

The Luminos Fund has been named a top 10...

Well-planned cities essential for a resilient future in Africa concludes the World Urban Forum

The World Urban Forum (WUF) concluded today with a...

Private sector deemed key to unlocking AfCFTA potential

The private sector’s role is vital to fully unlock...

“Country Ownership Begins with Women’s Leadership”

In Ethiopia’s ongoing effort to strengthen its health system,...

Gebeya and PROFF-IT (VukaOS) Forge Strategic Alliance to Redefine African Startup Creation

Gebeya Inc., the pan-African Al technology company behind Dala...

UN Secretary-General backs South Africa’s work to establish an International Panel on Inequality

The Secretary-General of the United Nations, Antonio Guterres, has...

ECA hosts five-day workshop to strengthen Ethiopia’s capital markets

The United Nations Economic Commission for Africa (ECA) has...

840,000 deaths a year linked to psychosocial risks at work, ILO report finds

More than 840,000 people die each year from health...

Ethiopia receives €110 million from EIB Global to support agri-finance, with focus on women

The European Investment Bank’s international development arm, EIB Global,...
spot_img

Related Articles

Popular Categories

spot_imgspot_img