Wednesday, April 1, 2026

በአልኮል እና በትምባሆ ላይ የሚጣለው ‘የጤና ተኮር ታክስ’ ለሕክምና አገልግሎት ድጎማ ሊውል ነው

የኢትዮጵያ መንግሥት በጤናው ዘርፍ የሚያደርገውን የገንዘብ ድጋፍ ለማሳደግ እና በዜጎች ላይ የሚደርሰውን የሕክምና ወጪ ጫና ለመቀነስ፣ በአልኮል፣ በትምባሆ እና በስኳር በበለጸጉ መጠጦች ላይ የሚጣለውን የታክስ ገቢ ለጤናው ዘርፍ ድጎማ እንዲውል ለማድረግ ማቀዱ ተገለፀ።

“ናሽናል ኸልዝ ኮምፓክት” በተሰኘው የዓለም ባንክ ሪፖርት መሰረት፣ “የኃጢአት ታክስ” (Sin Tax) ተብለው በሚጠሩት በእነዚህ ምርቶች ላይ የሚጣለው የቀረጥ ጭማሪ በቀጥታ ወደ ጤናው ዘርፍ እንዲፈስ ይደረጋል።

ከዚህ የሚገኘው ገቢ በዋነኝነት ለማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድን ድጎማ የሚውል ሲሆን፣ ዓላማውም አነስተኛ ገቢ ያላቸው እና ተጋላጭ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎችን የሕክምና ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ነው።

ይህ አሰራር ተግባራዊ መደረጉ በዜጎች ላይ የሚደርሰውን ከፍተኛ የፋይናንስ ጫና በእጅጉ እንደሚቀንሰው ይጠበቃል።

በአሁኑ ወቅት ታካሚዎች ለሕክምና አገልግሎት ከኪሳቸው የሚያወጡት ቀጥተኛ ወጪ 39 በመቶ የሚሸፍን ሲሆን፣ በመንግሥት ድጎማ እና በታክስ ገቢው ዕገዛ እ.ኤ.አ በ2030 ይህንን ወጪ ወደ 20 በመቶ ዝቅ ለማድረግ ታቅዷል።

በተመሳሳይ ጊዜ የማህበረሰብ አቀፍ የጤና መድን ሽፋንን አሁን ካለበት 50 በመቶ ወደ 75 በመቶ ለማሳደግ የተያዘውን ግብ ለማሳካት ይህ የታክስ ገቢ እንደ ዋነኛ የፋይናንስ ምንጭ ያገለግላል።

ከገንዘብ ማሰባሰቡ ባሻገር፣ ይህ ስትራቴጂ መንግሥት ለጤናው ዘርፍ የሚመድበውን በጀት ለማሳደግ ካለው ቁርጠኝነት ጋር የተያያዘ ነው።

ኢትዮጵያ በጤናው ዘርፍ የነበረባትን የውጭ ዕርዳታ ጥገኝነት በግማሽ በመቀነስ የሀገር ውስጥ የሀብት አሰባሰብን ለማጠናከር እየሰራች ሲሆን፣ እስከ 2030 ድረስ አጠቃላይ የጤና ወጪን 8.3 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ አልማለች።

ይህ የታክስ ማሻሻያ ውጤታማ በሆነ መንገድ ከተተገበረ፣ ለጤናው ዘርፍ ዘላቂ የገንዘብ ምንጭ ከመሆኑ ባለፈ፣ ጎጂ የሆኑ ምርቶች በህብረተሰቡ ጤና ላይ የሚያደርሱትን ጉዳት ለመቀነስ እንደ ትልቅ መፍትሔ እንደሚቆጠር ሪፖርቱ አመልክቷል።

Hot this week

Production up, but the ‘cost’ variable weighs heavily

Production is up in 2021 for the Italian agricultural...

Luminos Fund’s catch-up education programs in Ethiopia recognized

The Luminos Fund has been named a top 10...

Well-planned cities essential for a resilient future in Africa concludes the World Urban Forum

The World Urban Forum (WUF) concluded today with a...

Private sector deemed key to unlocking AfCFTA potential

The private sector’s role is vital to fully unlock...

Container Shortage Reported Due to Maritime Transport Disruptions

The Ethiopian Maritime Authority (EMA) has announced a shortage...

Ethiopia’s MPC Holds Off on Lifting Credit Cap, Citing Global Uncertainty

The Monetary Policy Committee (MPC) of the National Bank...

Over 180,000 Metric Tons of Fuel Failed to Arrive Due to Conflict

Minister of Trade and Regional Integration (MoTRI) , Kassahun...

Ethiopia,China Reach Final Stage of Strategic Debt Restructuring Negotiations in Beijing

A high-level Ethiopian delegation, led by Finance Minister Ahmed...

Rejoinder: Language, Identity, and the State — A Clarification

Much of the criticism directed at my argument rests...

The Satellite Saw It First: When a Distant Conflict Froze Ethiopia’s Economy

(This piece draws on preliminary findings from an ongoing...

Name:Endrias Esrael

2. Education: (የት/ት ደረጃ)     BSC in Economics 3. Company name: (የመስሪያ...
spot_img

Related Articles

Popular Categories

spot_imgspot_img