Tuesday, March 3, 2026

ምክር ቤቱ ከ55 ዓመታት በኋላ የተሻሻለውን የዕፅዋት ጥበቃና ኳራንታይን አዋጅ አጸደቀ

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባኤ፤ ለግማሽ ክፍለ ዘመን ያህል ሲሰራበት የቆየውንና ኋላ ቀር የሆነውን የእፅዋት ጥበቃና ኳራንታይን አዋጅ የሚያሻሽል አዲስ ረቂቅ አዋጅ በሙሉ ድምፅ አፅድቋል።

ይህ አዲስ የጸደቀው አዋጅ ቁጥር 1400/2018 ሆኖ የሚመዘገብ ሲሆን፣ ዋነኛ ዓላማውም የሥነ ሕይወት ዕፅዋት ብልሽትንና ብክነትን መከላከል እንዲሁም ዘመናዊ የተባይ መከላከልና መቆጣጠር ሥርዓትን መዘርጋት ነው።

የዕፅዋት ጥበቃና ኳራንታይን አዋጅ ከ55 ዓመታት በፊት ወደ ሥራ የገባ በመሆኑ ለወቅታዊ ቁጥጥር አመቺ ባለመሆኑ መሻሻሉ የግድ መሆኑ ተገልጿል።

በምክር ቤቱ የግብርና ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ባቀረበው ሪፖርት ላይ ሰፊ ውይይት የተደረገ ሲሆን፣ በአዲሱ አዋጅ መሠረት በዕፅዋት ላይ ጉዳት ያደረሰ ማንኛውም አካል ከ1 እስከ 5 ዓመት በሚደርስ እስራት እንዲቀጣ ተደንግጓል።

በተጨማሪም ተቆጣጣሪ አካላት የሕግ ጥሰት ሲፈፅሙ ወይም የጉቦ ተግባር ላይ ሲሰማሩ በቀጥታ በእስራት እንዲቀጡ መደረጉ ተገልጿል።

የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ አቶ ሰለሞን ላሌ እንደገለጹት፤ አዋጁ ደረጃውን የጠበቀ የተባይ አሰሳና ቅኝት ለማድረግ እንዲሁም ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የሀገሪቱን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ጉልህ ድርሻ ይኖረዋል።

Hot this week

Production up, but the ‘cost’ variable weighs heavily

Production is up in 2021 for the Italian agricultural...

Luminos Fund’s catch-up education programs in Ethiopia recognized

The Luminos Fund has been named a top 10...

Well-planned cities essential for a resilient future in Africa concludes the World Urban Forum

The World Urban Forum (WUF) concluded today with a...

Private sector deemed key to unlocking AfCFTA potential

The private sector’s role is vital to fully unlock...

The Napkin Curve and the Limits of Economic Policy

Few images in modern economics are as simple—or as...

GERD: Africa’s energy Project of the Year

The Grand Ethiopian Renaissance Dam (GERD) has reached a...

Yohannes Names Backroom Staff Following National Team Reappointment

Yohannes Sahle, who was recently reinstated as the head...

No More Midnight Transactions: Ethiopia Steps Into the Light

I remember sitting in my office in 2019 with...
spot_img

Related Articles

Popular Categories

spot_imgspot_img