Monday, August 31, 2026

አይኤምኤፍ ለኢትዮጵያ ተጨማሪ 261 ሚሊዮን ዶላር እንዲለቀቅ ወሰነ

የዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) የሥራ አስፈፃሚ ቦርድ በኢትዮጵያ እየተተገበረ ባለው የተራዘመ የብድር አቅርቦት ፕሮግራም ላይ አራተኛውን ግምገማ በማጠናቀቁ፤ አገሪቱ የ261 ሚሊዮን ዶላር ተጨማሪ ብድር እንድታገኝ መወሰኑን አስታወቀ።

ይህ ውሳኔ ኢትዮጵያ በፕሮግራሙ ሥር እስካሁን ያገኘችውን ጠቅላላ የገንዘብ መጠን ወደ 2.183 ቢሊዮን ዶላር ከፍ ያደረገው ሲሆን፣ ገንዘቡ አገሪቱ የውጭ ክፍያ ሚዛንና የበጀት ፍላጎቶቿን እንድታሟላ ይረዳታል።

የድርጅቱ ምክትል ማኔጂንግ ዳይሬክተር ናይጄል ክላርክ እንደገለጹት፣ የኢትዮጵያ መንግሥት በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳው መሠረት እያከናወናቸው ያሉት ማሻሻያዎች ከሚጠበቀው በላይ ውጤት እያሳዩ ይገኛሉ።

በተለይም የውጭ ምንዛሬ ገበያውን ለማዘመን የተወሰዱ እርምጃዎች፣ የኤክስፖርት ዕድገት፣ የታክስ ገቢ አሰባሰብ መሻሻል እና የዋጋ ግሽበት መቀነስ ለኢኮኖሚው መረጋጋት ተስፋ ሰጪ ውጤቶች መሆናቸውን ቦርዱ አረጋግጧል። ይሁን እንጂ ዘላቂ የኢኮኖሚ ዕድገት ለማምጣትና ድህነትን ለመቀነስ የማሻሻያ ሥራዎቹ በተመሳሳይ ፍጥነት መቀጠል እንዳለባቸው አሳስቧል።

ቦርዱ በውይይቱ ወቅት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሬ ገበያውን ይበልጥ ግልጽ ለማድረግና የባንኮችን የተጣራ የውጭ ምንዛሬ ክምችት ወደ ሕጋዊ ገደብ ለማምጣት እያደረገ ያለውን ጥረት አድንቋል።

ከዚሁ ጋር ተያይዞ ብሔራዊ ባንክ ከጨረታ ውጭ በውጭ ምንዛሬ ገበያው ውስጥ ጣልቃ እንዳይገባ የሚከለክል አዲስ መመሪያ መካተቱ ተገልጿል።

የኢትዮጵያ መንግሥት የበጀት ጉድለቱን ለመቆጣጠር፣ የታክስ መሠረቱን ለማስፋት እና የነዳጅ ድጎማን በሂደት ለማንሳት የገባውን ቃል ተግባራዊ ማድረጉ የበጀት ጥንካሬን ለመመለስ ወሳኝ መሆኑም በመግለጫው ተመልክቷል።

በመጨረሻም፣ ኢትዮጵያ ከብድር አበዳሪ አገራት (OCC) ጋር የደረሰችው የመግባቢያ ስምምነት አበረታች መሆኑን የጠቀሰው አይ ኤም ኤፍ፣ ከግል አበዳሪዎች ጋር የሚደረገው ድርድር ተጠናክሮ እንዲቀጥል መክሯል።

አገሪቱ አዳዲስ የንግድ ብድሮችን ከመውሰድ በመቆጠብና ቅድሚያ ለልማት ፕሮጀክቶች ትኩረት በመስጠት የብድር ጫናዋን እንድታቃልልም ድርጅቱ ጥሪ አቅርቧል።

Hot this week

Production up, but the ‘cost’ variable weighs heavily

Production is up in 2021 for the Italian agricultural...

Luminos Fund’s catch-up education programs in Ethiopia recognized

The Luminos Fund has been named a top 10...

Well-planned cities essential for a resilient future in Africa concludes the World Urban Forum

The World Urban Forum (WUF) concluded today with a...

Private sector deemed key to unlocking AfCFTA potential

The private sector’s role is vital to fully unlock...

EPSS wins gold award at Fifth Africa Supply Chain Excellence Awards

The Ethiopian Pharmaceutical Supply Service (EPSS) has won the...

REQUEST FOR EXPRESSION OF INTEREST (EOI)

This notice is placed by UNECA. The accuracy, reliability...

REQUEST FOR EXPRESSION OF INTEREST (EOI)

This notice is placed by UNECA. The accuracy, reliability...

INVITATION FOR OPEN BID

National Bank of Ethiopia invites interested and eligible bidders...

INITIATIVE AFRICA (IA)CALL FOR CONSULTANCY SERVICES

Baseline Study ConsultantCSIF II Consortium-Wide Baseline Study Initiative Africa (IA),...

Advertisement Open for LOCAL Procurement

Topic- UNICEF (Ethiopia) wishes to request eligible bidders to...

Tender Notice

The Office of the United Nations High Commissioner for...

Regional implementation failures turn new compensation proclamation into new bottleneck

Ethiopian Electric Power (EEP) has revealed that ongoing and...
spot_img

Related Articles

Popular Categories

spot_imgspot_img