Thursday, April 16, 2026

አይኤምኤፍ ለኢትዮጵያ ተጨማሪ 261 ሚሊዮን ዶላር እንዲለቀቅ ወሰነ

የዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) የሥራ አስፈፃሚ ቦርድ በኢትዮጵያ እየተተገበረ ባለው የተራዘመ የብድር አቅርቦት ፕሮግራም ላይ አራተኛውን ግምገማ በማጠናቀቁ፤ አገሪቱ የ261 ሚሊዮን ዶላር ተጨማሪ ብድር እንድታገኝ መወሰኑን አስታወቀ።

ይህ ውሳኔ ኢትዮጵያ በፕሮግራሙ ሥር እስካሁን ያገኘችውን ጠቅላላ የገንዘብ መጠን ወደ 2.183 ቢሊዮን ዶላር ከፍ ያደረገው ሲሆን፣ ገንዘቡ አገሪቱ የውጭ ክፍያ ሚዛንና የበጀት ፍላጎቶቿን እንድታሟላ ይረዳታል።

የድርጅቱ ምክትል ማኔጂንግ ዳይሬክተር ናይጄል ክላርክ እንደገለጹት፣ የኢትዮጵያ መንግሥት በሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ አጀንዳው መሠረት እያከናወናቸው ያሉት ማሻሻያዎች ከሚጠበቀው በላይ ውጤት እያሳዩ ይገኛሉ።

በተለይም የውጭ ምንዛሬ ገበያውን ለማዘመን የተወሰዱ እርምጃዎች፣ የኤክስፖርት ዕድገት፣ የታክስ ገቢ አሰባሰብ መሻሻል እና የዋጋ ግሽበት መቀነስ ለኢኮኖሚው መረጋጋት ተስፋ ሰጪ ውጤቶች መሆናቸውን ቦርዱ አረጋግጧል። ይሁን እንጂ ዘላቂ የኢኮኖሚ ዕድገት ለማምጣትና ድህነትን ለመቀነስ የማሻሻያ ሥራዎቹ በተመሳሳይ ፍጥነት መቀጠል እንዳለባቸው አሳስቧል።

ቦርዱ በውይይቱ ወቅት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሬ ገበያውን ይበልጥ ግልጽ ለማድረግና የባንኮችን የተጣራ የውጭ ምንዛሬ ክምችት ወደ ሕጋዊ ገደብ ለማምጣት እያደረገ ያለውን ጥረት አድንቋል።

ከዚሁ ጋር ተያይዞ ብሔራዊ ባንክ ከጨረታ ውጭ በውጭ ምንዛሬ ገበያው ውስጥ ጣልቃ እንዳይገባ የሚከለክል አዲስ መመሪያ መካተቱ ተገልጿል።

የኢትዮጵያ መንግሥት የበጀት ጉድለቱን ለመቆጣጠር፣ የታክስ መሠረቱን ለማስፋት እና የነዳጅ ድጎማን በሂደት ለማንሳት የገባውን ቃል ተግባራዊ ማድረጉ የበጀት ጥንካሬን ለመመለስ ወሳኝ መሆኑም በመግለጫው ተመልክቷል።

በመጨረሻም፣ ኢትዮጵያ ከብድር አበዳሪ አገራት (OCC) ጋር የደረሰችው የመግባቢያ ስምምነት አበረታች መሆኑን የጠቀሰው አይ ኤም ኤፍ፣ ከግል አበዳሪዎች ጋር የሚደረገው ድርድር ተጠናክሮ እንዲቀጥል መክሯል።

አገሪቱ አዳዲስ የንግድ ብድሮችን ከመውሰድ በመቆጠብና ቅድሚያ ለልማት ፕሮጀክቶች ትኩረት በመስጠት የብድር ጫናዋን እንድታቃልልም ድርጅቱ ጥሪ አቅርቧል።

Hot this week

Production up, but the ‘cost’ variable weighs heavily

Production is up in 2021 for the Italian agricultural...

Luminos Fund’s catch-up education programs in Ethiopia recognized

The Luminos Fund has been named a top 10...

Well-planned cities essential for a resilient future in Africa concludes the World Urban Forum

The World Urban Forum (WUF) concluded today with a...

Private sector deemed key to unlocking AfCFTA potential

The private sector’s role is vital to fully unlock...

Renowned artist and educator Behailu Bezabih passes at 66

Ethiopia’s art community is mourning the loss of Behailu...

Black Sea imports outpace local supply as Ethiopia battles tight grain markets

Ethiopia’s agricultural sector is navigating a complex paradox of...

Afri Fund Capital eyes $6 billion raise for Lapsset project

Nairobi -based Afri Fund Capital has announced an ambitious...

Sudan and Ethiopia agree to boost air connectivity

Sudan and Ethiopia have moved to renew civil aviation...

AI is fuelling the ‘Digital Colonisation’ of Africa, warns UN Scientist

The United Nations has launched its first global panel...

Parliament approves law allowing companies, NGOs to provide farm services

The House of Peoples’ Representatives has cleared a law...

Ringleader of suspected human trafficking network arrested in Ethiopia

Police have arrested a man accused of being at...

37 mln voters registered for Ethiopia’s upcoming general election

The National Election Board of Ethiopia (NEBE) has announced...
spot_img

Related Articles

Popular Categories

spot_imgspot_img