Thursday, March 12, 2026

በኢትዮጵያ የሚገኘውን የኩርሙክ ወርቅ ማዕድን የሚያለማው አላይድ ጎልድ በ5.5 ቢሊዮን የካናዳ ዶላር ሊሸጥ ነው

በኢትዮጵያ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚገኘውን ግዙፉን የኩርሙክ የወርቅ ማዕድን ፕሮጀክት ጨምሮ በአፍሪካ ሦስት ዋና ዋና ይዞታዎች ያሉት አላይድ ጎልድ ኮርፖሬሽን በቻይናው የማዕድን ግዙፍ ዚጂን ጎልድ ለመገዛት ስምምነት ላይ መድረሱን አስታወቀ።

ካፒታል ጋዜጣ ዛሬ ጥር 18 ቀን 2018 ዓ.ም. ከወጣው መረጃ ላይ እንደተመለከተው፣ ዚጂን ጎልድ አላይድ ጎልድን በ5.5 ቢሊዮን የካናዳ ዶላር (በግምት 4 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር) በጥሬ ገንዘብ ለመግዛት የመጨረሻ ስምምነት ተፈራርሟል። ይህ ግብይት በአፍሪካ የማዕድን ዘርፍ በዓመቱ ከተመዘገቡት ትልልቅ ግዥዎች አንዱ ሆኖ ተመዝግቧል።

በሆንግ ኮንግ የአክሲዮን ገበያ የተመዘገበውና የገበያ ዋጋው በግምት 70 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር የሆነው ግዙፉ ዚጂን ጎልድ፣ በዚህ ግዥ አማካኝነት በአፍሪካ ያለውን ተደራሽነት በከፍተኛ ሁኔታ ያጠናክራል ተብሏል።

በስምምነቱ መሠረት ዚጂን ጎልድ ለእያንዳንዱ የአላይድ ጎልድ አክሲዮን 44 የካናዳ ዶላር በጥሬ ገንዘብ የሚከፍል ሲሆን፣ ይህም ኩባንያው ባለፉት 30 ቀናት በገበያ ላይ ከነበረው አማካይ ዋጋ የ27 በመቶ ብልጫ አለው። ይህ ከፍተኛ ዋጋ የቀረበው አላይድ ጎልድ ላለፉት ሁለት ዓመታት ሲያካሂድ የነበረው ስትራቴጂካዊ የንግድ ክለሳ ውጤት መሆኑ ተገልጿል።

የዚጂን ጎልድ ሊቀመንበር ሆንግፉ ሊን እንደገለጹት፣ ይህ ግዥ ኩባንያቸው በአፍሪካ ያለውን ተጽዕኖ በከፍተኛ ሁኔታ ያሳድገዋል። በተለይም በኢትዮጵያ የሚገኘውን የኩርሙክ ወርቅ ፕሮጀክት እና በማሊ የሚገኘውን የሳዲዮላ ፕሮጀክት ለብዙ አሥርተ ዓመታት ምርት የሚሰጡ “የትውልድ ሀብቶች” ሲሉ ጠርተዋቸዋል።

ሊቀመንበሩ አክለውም “እንደ አዲስ ባለቤት፣ በኢትዮጵያ፣ በማሊ እና በኮትዲቩዋር ከሚገኙ ባለድርሻ አካላት ጋር እነዚህን ፕሮጀክቶች የበለጠ ለማሳደግ በጉጉት እንጠብቃለን” ብለዋል።

የአላይድ ጎልድ ሊቀመንበርና ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፒተር ማሮን በበኩላቸው፣ “ይህ ግብይት ለአክሲዮን ባለቤቶቻችን ከፍተኛና ፈጣን የጥሬ ገንዘብ ጥቅም የሚያስገኝ ነው” ብለዋል። ግዥው ኩባንያው በአፍሪካ የገነባው ዓለም አቀፍ ደረጃ ያለው የማዕድን ይዞታ ውጤታማ መሆኑን የሚያረጋግጥ እንደሆነም ገልጸዋል።

ግዥው ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ የሚመነዘረው እስከ ሚያዝያ 2026 መጨረሻ ድረስ ይሆናል። ይሁን እንጂ ስምምነቱ እንዲጠናቀቅ የአላይድ ጎልድ ባለአክሲዮኖች በልዩ ስብሰባ በ66.6 በመቶ ድምፅ ግዥውን ማጽደቅ ይኖርባቸዋል።

ከዚህ በተጨማሪም የካናዳ ፍርድ ቤት እና የኢንቨስትመንት ቁጥጥር ተቋማት ፈቃድ ማግኘት እና የኢትዮጵያ፣ የማሊ እና የኮትዲቩዋር መንግስታት እንዲሁም የቻይና የቁጥጥር ተቋማት ይሁንታ እንደሚያስፈልግ ተገልጿል።

ግብይቱ እንደተጠናቀቀ አላይድ ጎልድ በቶሮንቶ እና በኒውዮርክ የአክሲዮን ገበያዎች የነበረው ምዝገባ የሚሰረዝ ሲሆን፣ ኩባንያው ሙሉ በሙሉ በዚጂን ጎልድ ስር ሆኖ ሥራውን ይቀጥላል።

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ግንባታው በመጠናቀቅ ላይ ያለው ኩርሙክ ወርቅ፣ ኢትዮጵያ በወርቅ ልማት የዓለም ካርታን እንደምትቀላቀል ማሳያ ሆኗል። ኩርሙክ ወርቅ ለ12 ዓመታት ወርቅ ማልማት የሚያስችል ክምችት ያለው ሲሆን፣ በዓመት እስከ 9 ቶን በላይ ወርቅ እንደሚያመርት ይጠበቃል።

ከ500 ሚሊዮን ዶላር በላይ ኢንቨስት እየተደረገበት ያለው ይህ ፕሮጀክት በቅርቡ ወደ ማምረት እንደሚገባ ይጠበቃል።

Hot this week

Production up, but the ‘cost’ variable weighs heavily

Production is up in 2021 for the Italian agricultural...

Luminos Fund’s catch-up education programs in Ethiopia recognized

The Luminos Fund has been named a top 10...

Well-planned cities essential for a resilient future in Africa concludes the World Urban Forum

The World Urban Forum (WUF) concluded today with a...

Private sector deemed key to unlocking AfCFTA potential

The private sector’s role is vital to fully unlock...

Ethiopia Emerges as East Africa’s Hotel Construction Powerhouse

Ethiopia has positioned itself as one of Africa's most...

Somali  Regional  Education   Bureau  Invitation   for National  Competitive   Bid

Somali  Regional Education  Bureau invites  interested eligible  bidders  invites...

Sandford International School

Admission of National Students for Nursery, Reception, and Year...

Call for Audit Proposal

RTI International is an independent, nonprofit research institute dedicated...

Invitation for BID

RTI is an independent organization dedicated to conducting innovative,...

Invitation for BID

RTI is an independent organization dedicated to conducting innovative,...
spot_img

Related Articles

Popular Categories

spot_imgspot_img