Saturday, April 4, 2026

መንግሥት በነዳጅ ላይ ሲያደርግ የነበረውን ድጎማ እስከ መጪው የካቲት ወር ሙሉ በሙሉ ሊያነሳ ነው

መንግሥት ላለፉት አራት ዓመታት በነዳጅ ምርቶች ላይ ሲያደርግ የነበረውን ድጎማ በከፍተኛ ሁኔታ በመቀነስ፣ እስከ መጪው የካቲት 2018 ዓ.ም. መጨረሻ ድረስ ከድጎማ ሥርዓቱ ሙሉ በሙሉ እንደሚወጣ ካፒታል ያገኘዉ መረጃ አመልክቷል።

ይህ ውሳኔ መንግሥት ከዓለም አቀፍ የገንዘብ ተቋማት ጋር በገባው ቃል መሠረት የኢኮኖሚ ማሻሻያውን ተግባራዊ ለማድረግ የወሰደው እርምጃ አካል መሆኑ ለመረዳት ችሏል።

ባለሥልጣናቱ በገቡት ቃል መሠረት በዚህኛው የታኅሣሥ ወር መጀመሪያ ላይ አዲስ የዋጋ ጭማሪ ተግባራዊ አድርገዋል። በዚህም መሠረት ለተጠቃሚዎች የሚቀርበው የናፍጣ ዋጋ በ11 በመቶ፣ የቤንዚን ዋጋ ደግሞ በ5 በመቶ እንዲጨምር ተደርጓል።

ይህ ጭማሪ እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር ከ2025 መጀመሪያ አንስቶ በነዳጅ ውጤቶች ላይ የተደረገውን አጠቃላይ የዋጋ ጭማሪ በከፍተኛ ሁኔታ አሳድጎታል። ባለፉት አሥራ ሁለት ወራት ውስጥ ብቻ የናፍጣ ዋጋ በ43 በመቶ፣ የቤንዚን ዋጋ ደግሞ በ42 በመቶ የዋጋ ጭማሪ የታየባቸው ሲሆን፣ ይህም ድጎማውን ደረጃ በደረጃ የማንሳቱ ሂደት ውጤት መሆኑን ካፒታል ጋዜጣ ተመልክቷል።

መንግሥት ከ2014 ዓ.ም. ጀምሮ በሀገር ውስጥ የነዳጅ ዋጋ ላይ ሲያደርግ የነበረውን ጥቅል ድጎማ በሂደት በመቀነስ እስከ ሰኔ 2016 ዓ.ም. መጨረሻ ድረስ ከድጎማ ሥርዓት ሙሉ በሙሉ ለመውጣት አቅዶ እንደነበር ይታወሳል።

ይሁን እንጂ ዝቅተኛው የኅብረተሰብ ክፍል ከኑሮ ውድነት ጫና እንዲጠበቅ በሚል መንግሥት ከሐምሌ 2016 ዓ.ም. ጀምሮ እንደገና ጥቅል ድጎማ ማድረግ ጀምሮ ነበር።

ይህ የድጎማ አሠራር ከጎረቤት አገራት ጋር ያለውን የነዳጅ ዋጋ ልዩነት ሰፊ እንዲሆን በማድረጉ፣ ኮንትሮባንድና ሕገ-ወጥ ግብይት እንዲስፋፋ በር መክፈቱ ተገልጿል። ይህም በሀገር ሀብት ላይ ከፍተኛ ብክነት ከማስከተሉም በላይ በመንግሥት በጀት ላይ ሊሸከሙት የማይችሉት ጫና መፍጠሩን ባለሥልጣናቱ ይገልጻሉ።

ከነዳጅ ዋጋ ጭማሪ ጎን ለጎን፣ የኤሌክትሪክ ታሪፍ ማስተካከያም እየተተገበረ ይገኛል። በጥቅምት ወር 2025 (እ.ኤ.አ.) የተደረገው የኤሌክትሪክ ታሪፍ ጭማሪ በየሦስት ወሩ በሚደረገው የዘርፉ ማሻሻያ ዕቅድ መሠረት የተከናወነ ሲሆን፣ ይህም የኃይል አቅርቦት ተቋማት ራሳቸውን እንዲችሉ ለማድረግ ያለመ መሆኑ ታውቋል።

መንግሥት እስከ የካቲት 2026 (እ.ኤ.አ.) ድረስ የነዳጅ ድጎማን ሙሉ በሙሉ በማስቀረት፣ የሀገር ውስጥ የነዳጅ ግብይት በዓለም አቀፍ የገበያ ዋጋ መሠረት እንዲመራ ለማድረግ እየሠራ እንደሚገኝ ተገልጿል።

በኢያሱ ዘካሪያስ

Hot this week

Production up, but the ‘cost’ variable weighs heavily

Production is up in 2021 for the Italian agricultural...

Luminos Fund’s catch-up education programs in Ethiopia recognized

The Luminos Fund has been named a top 10...

Well-planned cities essential for a resilient future in Africa concludes the World Urban Forum

The World Urban Forum (WUF) concluded today with a...

Private sector deemed key to unlocking AfCFTA potential

The private sector’s role is vital to fully unlock...

Ethiopia, China ink deal for RMB trade settlements

To strengthen Ethiopia's financial resilience and further enhance economic...

​NEBE Warns of Election Cancellations Over Voter Registration Coercion

The National Election Board of Ethiopia (NEBE) has issued...

Bank of China, AfDB review financing framework for Bishoftu Airport

The Ethiopian Airlines Group and the Ministry of Finance...

Container Shortage Reported Due to Maritime Transport Disruptions

The Ethiopian Maritime Authority (EMA) has announced a shortage...

Ethiopia’s MPC Holds Off on Lifting Credit Cap, Citing Global Uncertainty

The Monetary Policy Committee (MPC) of the National Bank...

Over 180,000 Metric Tons of Fuel Failed to Arrive Due to Conflict

Minister of Trade and Regional Integration (MoTRI) , Kassahun...

Ethiopia,China Reach Final Stage of Strategic Debt Restructuring Negotiations in Beijing

A high-level Ethiopian delegation, led by Finance Minister Ahmed...
spot_img

Related Articles

Popular Categories

spot_imgspot_img