Saturday, December 13, 2025

ኢትዮጵያ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና የጉምሩክ ቀረጥ ቅናሽን በይፋ ተግባራዊ ማድረግ ጀመረች

ኢትዮጵያ ከአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና አባል ከሆኑ 24 አገራት ጋር የጉምሩክ ቀረጥ ቅናሽን በይፋ ተግባራዊ ማድረግ መጀመሯን ገልጻለች። ይህ እርምጃ አህጉራዊ የኢኮኖሚ ውህደትን በማጠናከር ረገድ ወሳኝ ምዕራፍ ተደርጎ ተወስዷል።

የጉምሩክ ቀረጥ ቅናሹ ሥራ ላይ የዋለው በሐምሌ 14 ቀን 2025 ዓ.ም. በፌዴራል ነጋሪት ጋዜጣ ላይ በታተመው ደንብ መሠረት ሲሆን ዓላማውም ከአፍሪካ አጋር አገራት ጋር በሚደረጉ የንግድ ልውውጦች ላይ ከ90% በላይ የሚሆኑ ሸቀጦች ላይ ያለውን የጉምሩክ ቀረጥ ሙሉ በሙሉ ለማስቀረት እንደሆነ ይታወቃል ።

የግምሩክ ኮሚሽን በቅርቡ ባስተላለፈው ሰርኩላር ደብዳቤ፣ የቀረጥ ቅናሹ የሚመለከተው ብሔራዊ መስፈርቶቻቸውን በማሟላት ለንግድ ቀጣናው ሴክሬታሪያት የንግድ ሃሳቦችን ያቀረቡትን 24 አገራት መሆኑን አሳውቋል። ከእነዚህም መካከል አልጀሪያ፣ ግብፅ፣ ጋና፣ ኬንያ፣ ሞሮኮ እና ሌሎችም ይገኙበታል።

መንግሥት ይህን ማበረታቻ ተግባራዊ ያደረገው ስምምነቱ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ፀድቆ ከሁለት ዓመት ገደማ በፊት በአፍሪካ ኅብረት ስብሰባ ላይ ይሁንታ ካገኘ በኋላ ነው።

መስከረም ወር 2018 መጨረሻ ላይ በይፋ ሥራ የጀመረው የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣ ፤ 55 የአፍሪካ አገራትን በአንድ ወጥ ገበያ ሥር ለማዋሃድ ያለመ ነዉ። ይህ ቀጠና 1.4 ቢሊዮን ሕዝብን እና 3.4 ትሪሊዮን የአሜሪካ ዶላር የሚሆን ጠቅላላ የአገር ውስጥ ምርትን እንደሚያጠቃልል ተመላክቷል።

Hot this week

Production up, but the ‘cost’ variable weighs heavily

Production is up in 2021 for the Italian agricultural...

Luminos Fund’s catch-up education programs in Ethiopia recognized

The Luminos Fund has been named a top 10...

Well-planned cities essential for a resilient future in Africa concludes the World Urban Forum

The World Urban Forum (WUF) concluded today with a...

Private sector deemed key to unlocking AfCFTA potential

The private sector’s role is vital to fully unlock...

የወጪ ንግድ ኮንትራት ምዝገባና የመላኪያ ፈቃድ አገልግሎት ከመጪው ሰኞ ጀምሮ በኦላይን ሊሆን ነዉ

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ለንግዱ ማኅበረሰብ የሚሰጠውን የሁለት ወሳኝ...

IMF Urges Ethiopia to Deepen Forex Reforms, Maintain Fiscal Discipline

The International Monetary Fund (IMF) has called on Ethiopia...

How Smarter Business Operations Lead to Long-Term Growth

You will find that most business owners spend the...

አይኤምኤፍ ለኢትዮጵያ 261 ሚሊዮን ዶላር እንዲለቀቅ የባለሞያዎች ደረጃ ስምምነት ላይ ደረሰ

ዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (አይኤምኤፍ) ከኢትዮጵያ ጋር በ3.4 ቢሊዮን...

ሁሉም ባንኮች አዲስ እና ነባር ሂሳቦችን ለማስተሳሰር ወደ VeriFayda 2 እንዲሸጋገሩ ተወሰነ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እና የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም፣ የፋይዳ ዲጂታል...

NBE orders financial institutions to link accounts with Fayda ID

The National Bank of Ethiopia (NBE) has ordered all...

TECNO’s AFCON-Ready AI Features Reflect a New Era in Mobile Sports Viewing

#Advertorial TECNO, official CAF global partner, introduces four intelligent tools...

Instant Payments, Big Data & High Availability: Why Banks in Ethiopia Need a Robust Data Backbone

By Demos Kyriacou Instant payments, big data and high availability...
spot_img

Related Articles

Popular Categories

spot_imgspot_img