Saturday, December 13, 2025

ኢትዮጵያ አየር መንገድ እና ፍላይዱባይ የሶማሊያ ኢ-ቪዛ ለሶማሊላንድ በረራዎች እንደማይሠራ አረጋገጡ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ እና ፍላይዱባይ (FlyDubai) ወደ ሶማሊላንድ ለሚደረጉ በረራዎች የጉዞ መመሪያዎቻቸውን በማዘመን፣ የሶማሊያ የኤሌክትሮኒክስ ቪዛ (ኢ-ቪዛ) መስፈርት በሃርጌሳ እና በበርበራ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያዎች ላይ እንደማይሠራ በይፋ አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ እንዳስታወቀው “የሶማሊያ የኢ-ቪዛ መስፈርቶች ወደ በርበራ ወይም ሃርጌሳ ለሚመጡ ተሳፋሪዎች አይሰራም” በማለት ገልጿል። አየር መንገዱ ወደ ሶማሊላንድ የሚጓዙ ተሳፋሪዎች ሲደርሱ ቪዛ ማግኘት እንደሚችሉ አፅንኦት ሰጥቷል።

ፍላይዱባይ በተመሳሳይ የጉዞ ማስጠንቀቂያውን በማሻሻል፣ መንገደኞች በሃርጌሳ እና በበርበራ ሲደርሱ ቪዛ ማግኘት እንደሚችሉ አረጋግጧል። ይህ እርምጃ ዓለም አቀፉ የአየር ትራንስፖርት ማህበር (IATA)ን ጨምሮ በርካታ አካላት የሶማሊላንድን የኢሚግሬሽን ቁጥጥር ከሶማሊያ ሥርዓት በመለየት የጉዞ መመሪያዎችን ካወጡ በኋላ የተወሰደ ነው።

ከዚህ በተጨማሪም የአየር መንገዶቹ መመሪያዎች መሻሻል የተከሰተው ዩናይትድ ስቴትስ በሶማሊያ የኢ-ቪዛ ሲስተም ላይ ትልቅ የደኅንነት ጥሰት ከተፈጸመ በኋላ ባወጣችዉ አስቸኳይ ማስጠንቀቂያ ነዉ።

በሶማሊያ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ እንዳረጋገጠው፣ ጠላፊዎች የሶማሊያን የኢ-ቪዛ መድረክ ሰብረው በመግባት ቢያንስ የ35,000 አመልካቾችን የግል መረጃ ተጋልጧል።

ከዚህ ከተጋለጡት መረጃዎች መካከል በሺዎች የሚቆጠሩ የአሜሪካ ዜጎችን ጨምሮ ስም፣ የፓስፖርት ፎቶዎች፣ የትውልድ ቀኖች፣ የኢሜይል አድራሻዎች እና የመኖሪያ አድራሻዎች ይገኙበታል ተብሏል።

የአሜሪካ መንግሥት የሶማሊያን ኢ-ቪዛ ሲስተም የተጠቀሙ ዜጎቹን በአስቸኳይ በአቅራቢያቸው የሚገኘውን ኤምባሲያቸውን እንዲያነጋግሩ እና ማንኛውንም አጠራጣሪ እንቅስቃሴ እንዲከታተሉ አሳስቧል።

ባለሞያዎች እንደሚሉት፣ በሶማሊያ ሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣን እና በሱማሊላንድ መንግስት መካከል በአቪዬሽን ቁጥጥር ዙሪያ የሚታየው ውጥረት በሁለቱ አካላት ስልጣን ላይ የሚደረግ የፖለቲካ ትግል ማሳያ ነው።

ለዚህ ዉጥረት መነሻዉ የሶማሊያ አቋም መላውን የአየር ክልል የመቆጣጠር ስልጣን የእኔ ነው የሚል ሲሆን፣ ይህንንም ለማስፈጸም ወደ ሀርጌሳ ለሚጓዙ ሁሉም ተሳፋሪዎች የሶማሊያ ኢ-ቪዛ እንዲኖራቸው አዟል። በሌላ በኩል፣ የሶማሊላንድ አቋም ደግሞ ራሷን የቻለች ሀገር በመሆኗ የአየር ክልሏን በሙሉ የመቆጣጠር መብት እንዳላት ትናገራለች።

በዚህ መሠረት፣ ዓለም አቀፍ አየር መንገዶች በሰማሊላንድ አየር ማረፊያዎች (እንደ ሀርጌሳ) ከማረፋቸው በፊት ከራሱ የክልል ባለሥልጣናት የቅድሚያ ፈቃድ እንዲያገኙ በማዘዝ፣ የሶማሊያን ኢ-ቪዛ ሕገ-ወጥ መሆኑን በመቃወም በአንድ ክልል ላይ የቁጥጥር ስልጣንን ለመጠየቅ የሚያደርጉትን ጥረት በተግባር እያሳዩ መሆኑ ተመላክቷል።

Hot this week

Production up, but the ‘cost’ variable weighs heavily

Production is up in 2021 for the Italian agricultural...

Luminos Fund’s catch-up education programs in Ethiopia recognized

The Luminos Fund has been named a top 10...

Well-planned cities essential for a resilient future in Africa concludes the World Urban Forum

The World Urban Forum (WUF) concluded today with a...

Private sector deemed key to unlocking AfCFTA potential

The private sector’s role is vital to fully unlock...

የወጪ ንግድ ኮንትራት ምዝገባና የመላኪያ ፈቃድ አገልግሎት ከመጪው ሰኞ ጀምሮ በኦላይን ሊሆን ነዉ

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ለንግዱ ማኅበረሰብ የሚሰጠውን የሁለት ወሳኝ...

IMF Urges Ethiopia to Deepen Forex Reforms, Maintain Fiscal Discipline

The International Monetary Fund (IMF) has called on Ethiopia...

How Smarter Business Operations Lead to Long-Term Growth

You will find that most business owners spend the...

አይኤምኤፍ ለኢትዮጵያ 261 ሚሊዮን ዶላር እንዲለቀቅ የባለሞያዎች ደረጃ ስምምነት ላይ ደረሰ

ዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም (አይኤምኤፍ) ከኢትዮጵያ ጋር በ3.4 ቢሊዮን...

ሁሉም ባንኮች አዲስ እና ነባር ሂሳቦችን ለማስተሳሰር ወደ VeriFayda 2 እንዲሸጋገሩ ተወሰነ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እና የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም፣ የፋይዳ ዲጂታል...

NBE orders financial institutions to link accounts with Fayda ID

The National Bank of Ethiopia (NBE) has ordered all...

TECNO’s AFCON-Ready AI Features Reflect a New Era in Mobile Sports Viewing

#Advertorial TECNO, official CAF global partner, introduces four intelligent tools...

Instant Payments, Big Data & High Availability: Why Banks in Ethiopia Need a Robust Data Backbone

By Demos Kyriacou Instant payments, big data and high availability...
spot_img

Related Articles

Popular Categories

spot_imgspot_img